• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዳውድ ኢብሣ ከህወሓት ጋር በማበርና በሌሎች ምክንያቶች ከሥልጣን ተወገዱ

September 14, 2020 08:30 am by Editor 1 Comment

“ሕወሓት በኦሮሞ ህዝብና ታጋዮች ላይ ላደረሰው ጉዳት ይቅርታ ካልጠየቀ ከፓርቲው ጋር ምንም ግንኙነት የለኝም” ሲል ኦነግ አስታወቀ። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሥራ አስፈጻሚ ድርጅቱን ለ21 ዓመት የመሩትን አቶ ዳውድ ኢብሳን ከሊቀመንበርነት ማንሳቱን ይፋ አድርጓል።

የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ቀጄላ መርዳሳ አቶ ዳዉድ ኢብሳ በሊቀመንበርነት በቆዩባቸው 21 ዓመታት “የድርጅቱን ገንዘብና ሀብት ብቻቸውን ሲያዙበት ኖረዋል ፤ በድርጅቱ ውስጥ አድልዎ በመፍጠር የአካባቢያቸውን ሰዎችና ዘመዶች ቁልፍ የስራ መደቦች ላይ በመመደብ ጥቅማቸውን አስጠብቀዋል” ሲሉ ለአል ዐይን ኒውስ ተናግረዋል። ግንባሩ የሊቀመንበሩን መታገድ በተመለከተ መግለጫም አውጥቷል።

መግለጫው አቶ ዳውድን “በዚህ መሰል ኣካሄድ ከድርጅቱ ህገ ደንብና አሰራር ውጭ የራሳቸውን አምባገነንነት በድርጅቱ ላይ አነግሰዋለ” ያለ ሲሆን “አቶ ዳዉድ ኢብሳ 21 ዓመት በሊቀ መንበርነት በቆዩበት ጊዜ ድርጅቱ ፈራርሶ ከነበረበት ወረደ እንጂ እድገት አላሳየም” ብሏል። አቶ ዳውድ በአመራር ዘመናቸው የኦነግ ዋና አመራርና መዋቅሩ እንዲፈርስ ማድረጋቸውንና የጋራ አመራር የሚለው በሃሳብ እንጂ በተግባር ሊታይ እንዳልቻለ ፓርቲያቸው ገልጿል።

አሁን ላይ ኦነግ ዉስጥ የተማሩና ልምድ የቀሰሙ አባላት ቁጥር አነስተኛ መሆኑን የገለጸው ግንባሩ ለዚህ ደግሞ “ተጠያቂው አቶ ዳዉድ ናቸው” ብሏል።

ግንባሩ ብዙ አመታት ባስቆጠረው የኦሮሞ ነጻነት ትግል ውስጥ ኦነግ ከተለያዩ ብሄርና ብሄረሰቦች ትግል ጋር የትግል አጋርነትና ወዳጅነት ለመፍጠር ጥረቶችእንዳደረገ ያነሳ ሲሆን ይህም የትግል አጋርነትና ወዳጅነት በእኩልነት፣ በመከባበርና በዲሞክራስያዊ መርህ ላይ መሆንን መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጿል።

ለታክቲክ ወይም ለግዜያዊ ጥቅም ተብሎ የሚደረግ ትብብር ዘለቄታዊ ጥቅም እንደማያስገኝ ያነሳው የግንባሩ መግለጫ በተለይም ሕወሓት በኦሮሞ ህዝብና በኦሮሞ ታጋዮች ላይ ላደረሰው ከፍተኛ ጉዳት ይቅርታ ጠይቆ በኦሮሞ ህዝብ ቅቡልነት አስኪያገኝ ድረስ ኦነግ ከዚህ ድርጅት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው መሆኑን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ይሁንና አቶ ዳዉድ ኢብሳ ከአመራሩ ዕውቅና ውጪ የፋይናንስ ሰራተኛቸውን በቅርቡ መቀሌ በተካሄደው የህወሃት ስብሰባ ላይ አንዲሳተፍና ግንኙነት እንዲያደርግ መላኩ የግንባሩን ፖሊሲ የጣሰ ህገ ወጥ ድርጊት መሆኑን ነው ፓርቲው የገለጸው። ኦነግ በኦሮሞና በትግራይ ህዝብ መካከል ያለው ወንድማዊና ዘላቂ ግንኙነት አንዲጠናከር እንደሚሰራም አስታውቋል።

ኦነግ ከተጋረጠበት አደጋ ለመታደግና ያለውን ድክመት ለማረም እንደሚሰራ የገለጸው መግለጫው ፣ “አቶ ዳውድ ኢብሳ ከድርጅቱና ከሀገሪቱ የፓርቲ ህግና ደንብ ውጪ እየተንቀሳቀሱ በመሆኑ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአቶ ዳውድን ህገ ወጥ እንቅስቃሴዎችን አንዲከታተል” ሲል ጥሪ አቅርቧል።

በመሆኑም “አቶ ዳውድ የኦነግ ሊቀ መንበር የሚል ስም በመጠቀም ከቦርዱና ከተለያዩ አካላት ጋር ግንኙነት ለማድረግ የሚያደርጓቸው ጥረቶች በድርጅቱ ተቀባይነት የላቸውም” ይላል መግለጫው። ግንባሩ ጠቅላላ ጉባዔ አድርጎ አዲስ መሪ እስኪመረጥ ድረስ ምክትል ሊቀ መንበሩ አቶ አራርሶ ቢቂላ የድርጅቱ ተወካይና መሪ እንዲሆኑ መወሰኑ በመግለጫው ላይ ሰፍሯል።

“ከኦነግ ከፍተኛ አመራር ውስጥ ሊቀ መንበሩ ያሰማሯቸው ጥቂት ግለሰቦች የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊትን መቀላቀላቸውና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሰራዊት ከፍተኛ አመራር በማለት በትጥቅ ትግል ለመቀጠል መርጠዋል” ያለው የኦነግ መግለጫ “ጥቂት አባላት በስልክ ሠራዊቱን ለመገናኘት መሞከርና የሰላማዊ ትግሉን ስነ ምግባር ያለማክበር ድርጅቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል” ሲል ገልጿል።

ይህም በተለይም በወለጋና ጉጂ የሚኖረው ህዝብ ላይ ከፍተኛ ወከባ፣ የሀገር ውስጥ ስደት፣ የህይወትና የንብረት ጉዳት በማስከተል የህዝቡን የመንቀሳቀስ ነጻነትና ሰላማዊ ኑሮ ማናጋቱን አስታውቋል።

በውጭ ያሉ ጥቂት የድርጅቱ አመራር አባላት የነበሩ ግለሰቦችም “ከትጥቅ ትግል ውጪ የሚያዋጣን የለም” በማለት ገንዘብ በማሰባሰብና በየጊዜው በማህበራዊ ሚዲያና በኦኤንኤን (ONN) ቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ወጥተው በኦነግ ስም የሚያስተላልፉት መልዕክትና የሚያደርጉት ቅስቀሳዎችና ጥሪዎች ከድርጅቱ የትግል ስትራቴጂና ከሀገሪቷ ህግ ጋር የሚጣረሱ በመሆናቸው” በድርጅቱ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳሳደረ በመግለጫው አካቷል።

“ከፊል የድርጅቱን የአመራር አባላት የትጥቅ ትግል ደጋፊዎች፣ ሌሎችን ደግሞ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የሚፈልጉና ከመንግስት ጋር ያበሩ በማለት የስም ማጥፋት ዘመቻ እያካሄዱ ራሳቸውን ወደር የማይገኝለት የነጻነት ታጋይ አስመስለው በማቅረብ በድርጅቱ ውስጥ መከፋፈል አንዲኖር በሰፊው ዘመቻ አካሂደዋል” ብሏል ግንባሩ ባወጣው መግለጫ።

ከዚህ ቀደም አቶ ዳውድ በጊዜያዊነት ስለመታገዳቸው አል ዐይን አማርኛ መዘገቡ ይታወሳል። አሁን ድርጅቱ ስላሳለፈባቸው ዉሳኔ እንዲሁም በተያያዥነት ስላወጣው መግለጫ አቶ ዳውድ ኢብሳን ለማናገር በእጅ ስልካቸው ላይ ለመደወል ብንሞክርም ስልካቸው ባለመስራቱ አል ዐይን ሀሳባቸውን ማካተት አልቻለም። (ምንጭ፤ አል ዐይን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News, Politics

Reader Interactions

Comments

  1. GI Haile says

    September 14, 2020 03:27 pm at 3:27 pm

    ራዕይ የሌለው መሪ በሆሮሞ ደም ሐብት ያፈራ ለማንም ግድ የሌለው ሰው ነው። ፀረ ሆሮሞ እንጅ ለሆሮሞ ሕዝብም ስለ ኢትዮጵያ አንድነት ደንታ የለውም። ዋናው ኣላማው ድርጅቱን ለራሱ በማድረግ ኣምባገነን ሆኖ ሆሮሞን ኣስፈጀ። መነሳት የተበረበት ከኣስር አመት በፊት ሆኖ ቢሆን ዛሬ ኢትዮጵያ ሆነ ሆሮምያ እንደዚህ ኣይነት ወንጀል በሆነግና በሸኔ ባልተሰራ ነበር። የተወሰደው እርምጃ ትክክለኛ ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • ሰብዓዊ እርዳታ ወደ መቀሌ መግባት መቀጠሉ ተገለጸ May 16, 2022 03:07 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule