• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዳውድ ኢብሣ ከህወሓት ጋር በማበርና በሌሎች ምክንያቶች ከሥልጣን ተወገዱ

September 14, 2020 08:30 am by Editor 1 Comment

“ሕወሓት በኦሮሞ ህዝብና ታጋዮች ላይ ላደረሰው ጉዳት ይቅርታ ካልጠየቀ ከፓርቲው ጋር ምንም ግንኙነት የለኝም” ሲል ኦነግ አስታወቀ። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሥራ አስፈጻሚ ድርጅቱን ለ21 ዓመት የመሩትን አቶ ዳውድ ኢብሳን ከሊቀመንበርነት ማንሳቱን ይፋ አድርጓል።

የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ቀጄላ መርዳሳ አቶ ዳዉድ ኢብሳ በሊቀመንበርነት በቆዩባቸው 21 ዓመታት “የድርጅቱን ገንዘብና ሀብት ብቻቸውን ሲያዙበት ኖረዋል ፤ በድርጅቱ ውስጥ አድልዎ በመፍጠር የአካባቢያቸውን ሰዎችና ዘመዶች ቁልፍ የስራ መደቦች ላይ በመመደብ ጥቅማቸውን አስጠብቀዋል” ሲሉ ለአል ዐይን ኒውስ ተናግረዋል። ግንባሩ የሊቀመንበሩን መታገድ በተመለከተ መግለጫም አውጥቷል።

መግለጫው አቶ ዳውድን “በዚህ መሰል ኣካሄድ ከድርጅቱ ህገ ደንብና አሰራር ውጭ የራሳቸውን አምባገነንነት በድርጅቱ ላይ አነግሰዋለ” ያለ ሲሆን “አቶ ዳዉድ ኢብሳ 21 ዓመት በሊቀ መንበርነት በቆዩበት ጊዜ ድርጅቱ ፈራርሶ ከነበረበት ወረደ እንጂ እድገት አላሳየም” ብሏል። አቶ ዳውድ በአመራር ዘመናቸው የኦነግ ዋና አመራርና መዋቅሩ እንዲፈርስ ማድረጋቸውንና የጋራ አመራር የሚለው በሃሳብ እንጂ በተግባር ሊታይ እንዳልቻለ ፓርቲያቸው ገልጿል።

አሁን ላይ ኦነግ ዉስጥ የተማሩና ልምድ የቀሰሙ አባላት ቁጥር አነስተኛ መሆኑን የገለጸው ግንባሩ ለዚህ ደግሞ “ተጠያቂው አቶ ዳዉድ ናቸው” ብሏል።

ግንባሩ ብዙ አመታት ባስቆጠረው የኦሮሞ ነጻነት ትግል ውስጥ ኦነግ ከተለያዩ ብሄርና ብሄረሰቦች ትግል ጋር የትግል አጋርነትና ወዳጅነት ለመፍጠር ጥረቶችእንዳደረገ ያነሳ ሲሆን ይህም የትግል አጋርነትና ወዳጅነት በእኩልነት፣ በመከባበርና በዲሞክራስያዊ መርህ ላይ መሆንን መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጿል።

ለታክቲክ ወይም ለግዜያዊ ጥቅም ተብሎ የሚደረግ ትብብር ዘለቄታዊ ጥቅም እንደማያስገኝ ያነሳው የግንባሩ መግለጫ በተለይም ሕወሓት በኦሮሞ ህዝብና በኦሮሞ ታጋዮች ላይ ላደረሰው ከፍተኛ ጉዳት ይቅርታ ጠይቆ በኦሮሞ ህዝብ ቅቡልነት አስኪያገኝ ድረስ ኦነግ ከዚህ ድርጅት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው መሆኑን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ይሁንና አቶ ዳዉድ ኢብሳ ከአመራሩ ዕውቅና ውጪ የፋይናንስ ሰራተኛቸውን በቅርቡ መቀሌ በተካሄደው የህወሃት ስብሰባ ላይ አንዲሳተፍና ግንኙነት እንዲያደርግ መላኩ የግንባሩን ፖሊሲ የጣሰ ህገ ወጥ ድርጊት መሆኑን ነው ፓርቲው የገለጸው። ኦነግ በኦሮሞና በትግራይ ህዝብ መካከል ያለው ወንድማዊና ዘላቂ ግንኙነት አንዲጠናከር እንደሚሰራም አስታውቋል።

ኦነግ ከተጋረጠበት አደጋ ለመታደግና ያለውን ድክመት ለማረም እንደሚሰራ የገለጸው መግለጫው ፣ “አቶ ዳውድ ኢብሳ ከድርጅቱና ከሀገሪቱ የፓርቲ ህግና ደንብ ውጪ እየተንቀሳቀሱ በመሆኑ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአቶ ዳውድን ህገ ወጥ እንቅስቃሴዎችን አንዲከታተል” ሲል ጥሪ አቅርቧል።

በመሆኑም “አቶ ዳውድ የኦነግ ሊቀ መንበር የሚል ስም በመጠቀም ከቦርዱና ከተለያዩ አካላት ጋር ግንኙነት ለማድረግ የሚያደርጓቸው ጥረቶች በድርጅቱ ተቀባይነት የላቸውም” ይላል መግለጫው። ግንባሩ ጠቅላላ ጉባዔ አድርጎ አዲስ መሪ እስኪመረጥ ድረስ ምክትል ሊቀ መንበሩ አቶ አራርሶ ቢቂላ የድርጅቱ ተወካይና መሪ እንዲሆኑ መወሰኑ በመግለጫው ላይ ሰፍሯል።

“ከኦነግ ከፍተኛ አመራር ውስጥ ሊቀ መንበሩ ያሰማሯቸው ጥቂት ግለሰቦች የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊትን መቀላቀላቸውና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሰራዊት ከፍተኛ አመራር በማለት በትጥቅ ትግል ለመቀጠል መርጠዋል” ያለው የኦነግ መግለጫ “ጥቂት አባላት በስልክ ሠራዊቱን ለመገናኘት መሞከርና የሰላማዊ ትግሉን ስነ ምግባር ያለማክበር ድርጅቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል” ሲል ገልጿል።

ይህም በተለይም በወለጋና ጉጂ የሚኖረው ህዝብ ላይ ከፍተኛ ወከባ፣ የሀገር ውስጥ ስደት፣ የህይወትና የንብረት ጉዳት በማስከተል የህዝቡን የመንቀሳቀስ ነጻነትና ሰላማዊ ኑሮ ማናጋቱን አስታውቋል።

በውጭ ያሉ ጥቂት የድርጅቱ አመራር አባላት የነበሩ ግለሰቦችም “ከትጥቅ ትግል ውጪ የሚያዋጣን የለም” በማለት ገንዘብ በማሰባሰብና በየጊዜው በማህበራዊ ሚዲያና በኦኤንኤን (ONN) ቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ወጥተው በኦነግ ስም የሚያስተላልፉት መልዕክትና የሚያደርጉት ቅስቀሳዎችና ጥሪዎች ከድርጅቱ የትግል ስትራቴጂና ከሀገሪቷ ህግ ጋር የሚጣረሱ በመሆናቸው” በድርጅቱ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳሳደረ በመግለጫው አካቷል።

“ከፊል የድርጅቱን የአመራር አባላት የትጥቅ ትግል ደጋፊዎች፣ ሌሎችን ደግሞ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የሚፈልጉና ከመንግስት ጋር ያበሩ በማለት የስም ማጥፋት ዘመቻ እያካሄዱ ራሳቸውን ወደር የማይገኝለት የነጻነት ታጋይ አስመስለው በማቅረብ በድርጅቱ ውስጥ መከፋፈል አንዲኖር በሰፊው ዘመቻ አካሂደዋል” ብሏል ግንባሩ ባወጣው መግለጫ።

ከዚህ ቀደም አቶ ዳውድ በጊዜያዊነት ስለመታገዳቸው አል ዐይን አማርኛ መዘገቡ ይታወሳል። አሁን ድርጅቱ ስላሳለፈባቸው ዉሳኔ እንዲሁም በተያያዥነት ስላወጣው መግለጫ አቶ ዳውድ ኢብሳን ለማናገር በእጅ ስልካቸው ላይ ለመደወል ብንሞክርም ስልካቸው ባለመስራቱ አል ዐይን ሀሳባቸውን ማካተት አልቻለም። (ምንጭ፤ አል ዐይን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics

Reader Interactions

Comments

  1. GI Haile says

    September 14, 2020 03:27 pm at 3:27 pm

    ራዕይ የሌለው መሪ በሆሮሞ ደም ሐብት ያፈራ ለማንም ግድ የሌለው ሰው ነው። ፀረ ሆሮሞ እንጅ ለሆሮሞ ሕዝብም ስለ ኢትዮጵያ አንድነት ደንታ የለውም። ዋናው ኣላማው ድርጅቱን ለራሱ በማድረግ ኣምባገነን ሆኖ ሆሮሞን ኣስፈጀ። መነሳት የተበረበት ከኣስር አመት በፊት ሆኖ ቢሆን ዛሬ ኢትዮጵያ ሆነ ሆሮምያ እንደዚህ ኣይነት ወንጀል በሆነግና በሸኔ ባልተሰራ ነበር። የተወሰደው እርምጃ ትክክለኛ ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule