• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመንግሥት ሚዲያዎች ፍትሃዊነታችንን አጉድላችሁብናል – ወ/ት ብርቱካን

July 11, 2021 08:41 pm by Editor 1 Comment

“ዛሬ እዚህ የምትቀርጹን የመንግስት ሚዲያዎች በጣም በትህትና ልነግራችሁ እፈልጋለሁኝ። የመንግስት ባለሥልጣናት ኮታቸው ላይ የተሰካው ማይክራፎን የማይወልቅ ይመስል ሌት ተቀን የእነሱን ካምፔን እና ቅስቀሳ ስታስተላልፉ ቆይታችሁ የተቃዋሚዎችን 10 እና 15 ደቂቃ ማድረጋችሁ ፍትሃዊነታችንን አጉድሎብናል። እንዳላየ ያለፍነው ግማሹ የኛ ሥልጣን ስላልሆነ ነው። የእኛን ስልጣን እንደምናከብር የሌሎችንም እናከብራለን” የምርጫ ውጤት በማሳወቂያ መርሃግብር ላይ ይህንን የተናገሩት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ናቸው።

ከዚህ በተጨማሪ ሰብሳቢዋ “ኢትዮጵያ ሁልጊዜ በምርጫ ብቻ ስልጣንን የምታሸጋግር አገር መሆኗን አሳይታለች” ብለዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የውጤት ማሳወቂያ መርኃ-ግብር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። መርኃ-ግብሩን በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ ምርጫው እንዲሳካ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ሁሉ ምስጋናቸውን ገልፀዋል።

የዛሬው መድረክም ቦርዱ የሰራቸውን ስራዎች የሚያስተዋውቅበት ብቻ ሳይሆን ከሂደቱ ሁሉም ትምህርት የሚያገኝበት እና ኢትዮጵያ ሁልጊዜ በምርጫ ብቻ ስልጣንን የምታሸጋግር አገር መሆኗ በድጋሚ የሚታይበት ሂደት ነው ብለዋል።

ምርጫው ቀላል በሚባል ሁኔታ ውስጥ የተደረገ አለመሆኑን ያስታወሱት የቦርዱ ዋና ሰብሳቢዋ ኢትዮጵያ በበርካታ ውጣውረዶች ውስጥ ሆና፣ ዜጎች በስጋት ውስጥ ሆነው ችግሮችን በመቋቋም ዛሬ ላይ ተደርሷል ብለዋል። ምርጫውን በመታዘብ የተሳተፉው 176 አባላት ያሉት የሲቪክ ማህበራት ህብረት ለምርጫ ሰብሳቢ አቶ ታምራት ከበደም በድምፅ መስጫ ቀን ለ2 ሺህ 400 በላይ ቋሚ እና ተንቀሳቃሽ ታዛቢዎችን በማሰማራት በ2 ሺህ 500 የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ለመታዘብ መቻሉን አስታውቀዋል።

የደባርቅ ምርጫ ክልል ኃላፊ የሆነችው ሳዲያ ዳውድም በመድረኩ ላይ ልጇን በጀርባዋ እንዳዘለች የነበራትን ልምድ ለተሳታፊዎች አጋርታለች።

በመድረኩ የምርጫ አስፈፃሚዎች የነበራቸውን ልምድ እና ያበረከቱትን አስተዋፅኦ ለተሳታፊዎቹ አብራርተዋል። የምርጫ ዝግጅት ሂደት ጀምሮ የምርጫ ቁሳቁስ በየምርጫ ጣቢያዎች እንዲደርስ ማድረግ ፈታኝ ስራ እንደነበር በምርጫ ቦርድ የመራጮች እና ስነ ዜጋ ትምህርት ክፍል ሀላፊዋ አርማዬ አሰፋ ተናግረዋል። የምርጫ ቦርድ ሰራተኞች የህዝብን አደራ ለመወጣት ሌት ተቀን በመስራት የኢትዮጵያን ጠንካራ የስራ ባህል አሳይተዋል ብለዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: birtukan midekssa, election 2013, election 2021

Reader Interactions

Comments

  1. ቆምጬ አምባው says

    July 13, 2021 02:37 pm at 2:37 pm

    And yet an another phoney calim:-

    “የእኛን ስልጣን እንደምናከብር የሌሎችንም እናከብራለን” የምርጫ ውጤት በማሳወቂያ መርሃግብር ላይ ይህንን የተናገሩት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ ሰብሳቢዋ “ኢትዮጵያ ሁልጊዜ በምርጫ ብቻ ስልጣንን የምታሸጋግር አገር መሆኗን አሳይታለች” ብለዋል። “

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule