ሰብለ (ሚሚ) ዲትሪች ለመጨረሻ ግዜ የታየችው እ.ኤ. አ. ጁላይ 10 2014 (ባለፈው አመት) ነበር። የሶስት ልጆች እናት የነበረች የዚህች ኢትዮጵያዊት በድንገት መሰወር ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኖ ሰንብቷል። ለአመት የጠፋችው ይህች ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሴት በህይወት እንደማትኖር በርካቶች ቢጠረጥሩም፣ ማንንም ሳታማክር በድብቅ ወደ ሃገርዋ ገብታለች የሚሉ አልጠፉም። አለም አቀፍ ፖሊስ በአለም ዙርያ ፍለጋውን ተያያዘው። በካናዳ ኪችነር ከተማ ቫንኮቨር ድራይቭ የተገኘው አጽም ግን የሁሉንም እንቆቅልሽ ፈታው። ሰብለ ህይወትዋ አልፏል። የሶስት ልጆችዋ አባት የነበረው ጀርመናዊው ስቴፋን ዲትሪች ገድሎ እዚያው መኖርያ ቤታቸው እንደቀበራት ፖሊስ ጠቁሟል። በፖሊስ እና በሰለጠኑ ውሾች ጥቆማ የተገኘው የሰብለ አስከሬን በቶሮንቶ ኮርነርስ ኮምፕለክስ ለጥናት ተልኮ የተገኘው ውጤት ሰብለ … [Read more...] about ጀርመናዊው የገደላት ሰብለ ከአንድ አመት በኋላ በመኖርያ ቤትዋ ተቀብራ ተገኘች
News
ዜና
ቴዲ በድጋሚ ፓስፖርቱን ተቀምቶ ነበር
ባለፈው ሳምንት ወደ ከአዲስ አበባ ናይሮቢ-ኬንያ ይጓዝ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራውን ከጀመረ በኋላ እንዲመለስ መደረጉን የአየር መንገዱ ምንጮች አስታወቁ። በዚህም ምክንያት አየር መንገዱ የሁለት መቶ ሺህ ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ምንጮቹ ጠቁመዋል። በተሳፋሪዎች ላይም ከፍተኛ መጉላላት ደርስዋል። አውሮፕላኑ ካኮበኮበ በኋላ እንዲመለስ የተደረገበት ምክንያት ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ ከባለቤቱ ከአለምሰት ሙጬ ጋር በአውሮፕላኑ በመሳፈሩ ምክንያት መሆኑ ተረጋግጧል። ይህ አስደንጋጭ ክስተት የተፈጸመው አለምሰት ሙጬ በደረሰባት ድንገተኛ ህመም ለህክምና ወደ ኬንያ እየተጓዘች ባለችበት አውሮፕላን ነው። አውሮፕላኑ ዞሮ ከተመለሰ በኋላም ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ በደህንነቶች ተይዞ ከአውሮፕላኑ እንዲወጣ ተደርጓል። የህወሃት የደህንነት አባላት የቴዲ አፍሮን ፓስፖርት ቀምተው አሰናብተውት … [Read more...] about ቴዲ በድጋሚ ፓስፖርቱን ተቀምቶ ነበር
ኢትዮጵያ ከ184 አገራት 171ኛዋ ደሃ አገር!
ዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የአምስት ዓመታት አኻዝ ያካተተ የዓለማችንን ሃብታምና ደሃ አገራት ዝርዝር ሰሞኑን አውጥቷል፡፡ የዓለም የፋይናንስ መጽሔት ላይ የታተመው ይኸው ዘገባ እንደሚያሳየው በሃብታምና ደሃ አገራት መካከል ያለው ልዩነት በእጅጉ እየጨመረ እንደመጣ ነው፡፡ በዚህ የአምስት ዓመት አኻዛዊ ዘገባ መሠረት ከ184 አገራት መካከል ኢትዮጵያ 171ኛ ተራ ላይ የምትገኝ ስትሆን ይህም በድህነት ከሚጠቀሱት ቀዳሚ አገራት ቁጥር ውስጥ አስገብቷታል፡፡ ዘገባውን የተመለከቱ የኢኮኖሚ ባለሙያ የአንድ አገር ኢኮኖሚ በከተሞች ውስጥ በሚሰራ ፎቅ ብዛት እና የመንገድ ሥራ አይለካም ይላሉ፡፡ ሌላ የኢኮኖሚ ባለሙያ ደግሞ “ኢኮኖሚ ከቁጥር ሌላ ሥነ ልቦናዊ ጉዳይም ነው፡፡ የኑሮ ጉዳይም ነው፡፡ የጉሮሮ ጉዳይም ነው፡፡ በቁጥር ብቻ አይለካም፡፡ … የሕንፃ መሐንዲስ ቢሳሳት ሕንፃ … [Read more...] about ኢትዮጵያ ከ184 አገራት 171ኛዋ ደሃ አገር!
ኢህአዴግ በኢንተርኔት ስለላ ተከሰሰ
የኢትዮጵያ መንግሥት ኮምፕዩተሬ ላይ “የስለላ ማልዌር ልኮብኝ ሲሰልለኝ ቆይቷል” ሲሉ ኪዳኔ ተብለው የተጠሩ አሜሪካዊ ዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ወረዳ ፍርድ ቤት ክሥ መሥርተው ጉዳዩ ትናንት ዳኛ ፊት ቀርቧል፡፡ የከሣሽና የተከሣሽ ጠበቆች ረዥም ክርክር አድርገዋል፡፡ የግለሰቦችን የግል ሕይወት ወይም ገመና መዳፈር፣ የስልክ ንግግሮቻቸውን ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ መጥለፍ፣ ኢሜሎቻቸውን ማንበብ ከአግባብ ውጭ፤ እንዲያውም ሕገወጥ የሆነ አድራጎት ነው ተብሎ ይበየንልን ሲሉ የኪዳኔ ጠበቃ ኔት ካርዶዞ ጠይቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ጠበቃ አድራጎቱን ፈፅሟል የተባለው የውጭ ሉዓላዊ መንግሥት በመሆኑ የዩናይትድ ስቴትስ ፍርድ ቤት ክሡን የማየት ሥልጣን የለውም ስለዚህም ችሎቱ ውድቅ ሊያደርገው ይገባል ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሃኪንግቲም የሚባለው ጣልያን የሚገኝ የስለላ … [Read more...] about ኢህአዴግ በኢንተርኔት ስለላ ተከሰሰ
የግፍ ሠንደቅ ወረደ!
በአሜሪካ የደቡብ ካሮላይና ጠቅላይ ግዛት ዋና ከተማ የሸንጎ ሕንጻ ላይ ከ50 በላይ ሲውለበለብ የነበረው ሠንደቅ አርብ ወረደ፡፡ “ውሸት ለዘላለም መቆየት አይችልም፤ የዘረኝነት ምልክት እና ዘረኝነት መፍረስ ይገባቸዋል” በማለት የሠንደቁን መውረድ የደገፉ ተናገሩ፡፡ በእንግሊዝኛው አጠራር “የኮንፌዴሬት” ሠንደቅ የሚባለው በአሜሪካ የእርስበርስ ጦርነት ወቅት ከኅብረቱ ለመለየት የፈለጉ ግዛቶች የራሳቸውን ፕሬዚዳንት መርጠው ከኅብረቱ ደጋፊዎችና አብርሃም ሊንከን ጋር ጦር በገጠሙበት የተጠቀሙበት ሠንደቅ ነው፡፡ ፕሬዚዳንት አብርሃም በአሜሪካ ውስጥ የተንሰራፋውን በዘር ላይ የተመሠረተውን ባርነት ለመደምሰስ ህግጋትን እያወጡ በነበሩበት ወቅት በባሪያ ፈንጋይነት የሚታወቁት የደቡብ ጠቅላይ ግዛቶች የባርነትን መወገድ በመቃወም ከኅብረቱ ለመገንጠል በመፈለጋቸው በአሜሪካ የእርስበርስ ጦርነት … [Read more...] about የግፍ ሠንደቅ ወረደ!
በኤርትራ ላይ ምርመራው እንዲቀጥል ተወሰነ
በኤርትራ ላይ የሚካሄደው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ምርመራ የሚጠረጠረውን በሰብዕና የሚፈፀም ወንጀል እንዲያካትት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ትናንት ወስኗል፡፡ ኤርትራ ውስጥ ያለውን የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ እንዲመረምር የተቋቋመው ልዩ አጣሪ ኮሚሽን ሥራውን በአንድ ዓመት እንዲያራዝም የተስማማው አርባ ሰባት አባላት ያሉት የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ክትትል አካል ነው፡፡ ምርመራው ሙሉ ተጠያቂነት ባለበት ሁኔታ እንዲካሄድ የምክር ቤቱ ውሣኔ አክሎ አሳስቧል፡፡ ኤርትራ ውስጥ ይፈፀማል የተባለውን ጅምላ የሰብዓዊ መብቶች ረገጣ የምክር ቤቱ የውሣኔ ሃሣብ ረቂቅ በአጀንዳነት እንዲያዝ ጥያቄ ያቀረቡት ጅቡቲና ሶማሊያ እንደሚያወግዙ አስታውቀዋል፡፡ የአውሮፓ ኅብረት የምርመራውን ጊዜ መራዘም “ኤርትራ ውስጥ እየተፈፀሙ ያሉ” ያላቸው የሰብዓዊ … [Read more...] about በኤርትራ ላይ ምርመራው እንዲቀጥል ተወሰነ
“ወንድ ከወንድ፤ ሴትም ከሴት ይጋቡ” ጠቅላይ ፍርድቤት
* “ፍቅር ፍቅር ነው” ኦባማ ወንድ ከወንድ፤ ሴትም ከሴት ጋር ጋብቻ መፈጸም ይችላሉ፤ ለእነርሱ የጋብቻ ሠርቲፊኬት መከልከል ሕገመንግሥቱን ይጥሳል በማለት የአሜሪካው ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መጋባት እንደሚችሉ ወሰነ፡፡ ለጋብቻ ቅድስናና ክቡርነት የሚከራከሩ “የእግዚአብሔርን ሕግ ምድራዊ ፍርድ ቤት ይህን መለወጥ አይችልም” በማለት ውሳኔውን አጥብቀው ተቃውመዋል፡፡ በምንም መልኩ ይገለጽ ፍቅር ፍቅር ነው በማለት ፕሬዚዳንት ኦባማ ውሳኔውን ደግፈዋል፡፡ ዋናውን (ዓቃቤ ፍትህ) ጨምሮ ዘጠኝ የፍትህ ዳኞች የያዘው የአሜሪካው ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዚህ የሰዶማውያን ጋብቻ ላይ ውሳኔ እንዲያስተላልፍ ጉዳዩ ከቀረበለት ጊዜያት ተቆጥረዋል፡፡ በአሜሪካ የፍትሕ ሥርዓት ምዕራፍ ከፋች የተባለለት ውሳኔ አርብ ዕለት ሲተላለፍ የፍትሕ ዳኞቹ በአምስት ለአራት በመወሰን ነው ያጸደቁት፡፡ … [Read more...] about “ወንድ ከወንድ፤ ሴትም ከሴት ይጋቡ” ጠቅላይ ፍርድቤት
የመድረክ ምርጫ አስተባባሪ በደቡብ ኢትዮጵያ ተደብድበው ተገደሉ
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ በደቡብ ክልል አንድ የምርጫ አስተባባሪው አርብለት ተገድለው መገኘታቸውን አስታወቀ። የተቃዋሚ ፓርቲም በምርጫ 2007 ዙሪያ የዛሬውን ጨምሮ 4 አባላቱና ደጋፊዎቹ መገደላቸውን አስታውቋል። በዚህ ሳምንት እንደተገደሉ ተቃዋሚዎች ከገለጿቸው ሶስት ሰዎች በተጨማሪ በኦሮሚያና ደቡብ ክልል ህይወታቸው ማለፉ የተገለጸው አጠቃላይ ቁጥር ስድስት ደርሷል። በደቡብ ክልል ሀዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ የተገደሉት አቶ ብርሃኑ ኤረቦ ሐሙስለት በሁለት ፖሊስ ባልደረቦች ከመኖሪያ ቤታቸው ከተወሰዱ በኋላ ተደብድበው ህይወታቸው አልፎ ወንዝ ዳር መገኘታቸውን የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ምርጫ 2005 በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ወደ 46ሽህ የሚጠጉ የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ሰላማዊ በሆነ መልኩ መከናወኑን የኢትዮጵያ መንግስትና ምርጫ ቦርድ … [Read more...] about የመድረክ ምርጫ አስተባባሪ በደቡብ ኢትዮጵያ ተደብድበው ተገደሉ
ኦባማ “የዕረፍት ጊዜ ለማሳለፍ” ወደ ኢትዮጵያ ይጓዛሉ
ዳግም የመመረጥ ጭንቀት በማይኖርበት በሁለተኛው የአስተዳደር ዘመን ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ እንደታየው የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች አፍሪካን ለዕረፍት ይጎበኛሉ፤ ይዝናናሉ፡፡ የዱር እንስሳትን ያያሉ፤ “የአገራቸውን ባህል ልብስ” ከለበሱ የአፍሪካ ሹመኞች ጋር ጥሩ ፎቶዎችን ይነሳሉ፤ የሥልጣን ዘመናቸው ካለቀ በኋላ ለሚመሠርቱት ቤተመጻህፍት ማስዋቢያ የሚሆን ለየት ያሉ ፎቶዎችን ይሰበስባሉ፡፡ መጪው ወር (July) መገባደጃ አካባቢ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለአራተኛ ጊዜ አፍሪካን እንደሚጎበኙ ቤተመንግሥታቸው አስታውቋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ በሚካሄድባት አዲስ አበባ ላይ በመገኘት ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የአባታቸው አገር ነው የሚባለውን ኬኒያ ለመጎብኘት አስቀድመው ዕቅድ የያዙት ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ የመምጣታቸው ጉዳይ አርብ ይፋ መደረጉ አስቀድሞ የታሰበ ሳይሆን … [Read more...] about ኦባማ “የዕረፍት ጊዜ ለማሳለፍ” ወደ ኢትዮጵያ ይጓዛሉ
“መሞቴ … የተሻለ ነው” አንዳርጋቸው
* “ልማታዊ ግድያውን” ተጠናክሮ ቀጥሏል እየሠራሁ ነው ለሚለው ልማትና ግድብ “እንደጀመርን እንጨርሰዋለን” እያለ የሚፈክረው ኢህአዴግ በየእስር ቤቱ የሚያሰቃያቸው ወገኖች ቁጥር እንዳለ ሆኖ “ልማታዊ ግድያውን” አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ሰሞኑን በግፍ የተገደለው ሳሙኤል አወቀን ጨምሮ ማክሰኞ ዕለት የዓረና-መድረክ አባል የሆኑት አቶ ታደሰ አብርሃ ታንቀው መገደላቸው ተሰማ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በሚያዚያ ወር በእንግሊዙ አምባሳደር የተጎበኙት አንዳርጋቸው ጽጌ ለመሞት ደስተኛ እንደሆኑና ምናልባትም የተሻለ መሆኑን ተናገሩ፡፡ የአቶ ታደሰ አብርሃን አገዳደል በፌስቡክ ገጹ ያሰራጨው አምዶም ገብረሥላሴ በዚህ መልኩ አቅርቦታል፡- አቶ ታደሰ አብርሃ የተባሉ የዓረና-መድረክ አባልና የምዕራባዊ ዞን የዓረና አመራር አባል ትናንት ማታ 09/10/2007 ዓ/ም በሶስት ሰዎች ታንቀው ተገደሉ። አቶ … [Read more...] about “መሞቴ … የተሻለ ነው” አንዳርጋቸው