ቀደም ሲል የአባትና ልጅ “አፈጣጠርና ግንኙነት” የነበራቸው ወዳጆች ሻዕቢያና ወያኔ ያልተጠናቀቀውን የባድመን ጦርነት ካካሄዱ በኋላ ለዳግም ግጥሚያ ዝግጅት እያደረጉ ነው። “የጦርነቱ ሁኔታ” ያሳሰበው ሻዕቢያ በማስታወቂያ መ/ቤቱ በኩል ለህወሃት ማጠንቀቂያ ሰጥቷል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በዘገበው መሠረት መግለጫው ህወሃት ኤርትራን እንዲወጋ የአሜሪካንን ይሁንታ አግኝቷል ብሏል። የፈረንጅ የቀን አቆጣጠር የሚከተለው ሻዕቢያ በማስታወቂያ መ/ቤቱ በኩል 4 September 2015 ያወጣው መረጃ እንደጠቆመው ህወሃት የተለመደውን የጦርነት አታሞ እየመታና ሳንጃ እየሳለ እንደሆነ ጠቁሟል። የህወሃት አገዛዝ “ሌሎች ክፍሎች ከኤርትራ ጋር እንዳይወግኑ ትንኮሳ እያደረገ” መሆኑን የጠቆመው መግለጫ ወያኔ በኤርትራ ጦርነት ማካሄድ እንዲችል ከአሜሪካ ይሁንታ ማግኘቱን በገሃድ … [Read more...] about ሻዕቢያ ህወሃትን አስጠነቀቀ
News
ዜና
ኦባማ “ልማታዊ” ጎብኚ?!
ለሁለት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደረጉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንትና አጃቢዎቻቸው ለሁለት ቀን አዳር ለሆቴል ያወጡት ወጪ ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ እንደነበር ተገለጸ፡፡ ፕሬዚዳንቱ በኢትዮጵያ የሚያደርጉት ጉብኝት በአንድ ሆቴል ብቻ እንደሚደረግ አስቀድሞ የተነገረ ቢሆንም የአስተዳደራቸው ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ አጃቢዎቻቸውና ሌሎች የደኅንነት ሠራተኞች በአራት ሆቴሎች ውስጥ አርፈው እንደነበር Weekly Standard የክፍያ ሰነዶችን በማስደገፍ ይፋ አድርጓል፡፡ አስቀድሞ የተለቀቀው መረጃ እንደሚያመለክተው የኦባማ ቡድን በሒልተን ሆቴል ቆይታ እንደሚያደርግና ወጪውም ብር 8,491,127.81 ወይም በግምት ዶላር $ 412,390.86 መሆኑን የሚያሳይ የኮንትራት ውል መፈረሙን ነበር፡፡ ከአሜሪካ መንግሥት የተጠያቂነት ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው የፕሬዚዳንቱ ቡድን ለሁለት ቀናት … [Read more...] about ኦባማ “ልማታዊ” ጎብኚ?!
በአፋር የተከሰተው የዝናብ እጥረት ያስከተለው ጉዳት
በሚሌ ወረዳ የሀርሲስ ቀበሌ ነዋሪዎች በድርቅ መጎዳታቸውን የአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ዘጋቢ ግርማይ ጋብሩ በአፋር ክልል ተዘዋውሮ ዘግቧል። ነዋሪዎቹንና የአፋር ክልል የመንግስት ባለስልጣኖችንም አነጋሯል። የሞቱ እንስሳት እንዳየና በህይወት የተረፉትም በምግብና በውሀ እጥረት ምክንያት እጅግ የተዳከሙ መሆናችውን ግርማይ ገብሩ ገልጾልናል። መንግስት በበኩሉ ምግብና ውሀ እያቀረበ መሆኑን በሰመራ የክልሉ የአደጋ ዝግጁነትና የምግብ ዋስትና ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ዐይሻ መሐመድ እንደገለጹ በዘገባው ጠቅሷል። (ሰሞኑን ከውጭ የመጡ ኢትዮጵያውያንን እያግባባ ያለው ኢህአዴግ የድርቁ ጉዳይ አሳስቦታል። ድርብ አሃዝ ዕድገት እየተባለ ሲሰበክ የነበረው ሁሉ ማጣፊያው ከመጠን በላይ አጥሮዋል። "ዴሞክራሲያዊ ፍትሃዊ እና ተዓማኒ የነበረውን ምርጫ" እንዳያበላሽ የተፈራው ድርቅ አፍንግጦ ወጥቶዋል። … [Read more...] about በአፋር የተከሰተው የዝናብ እጥረት ያስከተለው ጉዳት
በአፋር በየቀኑ እስከ 100 የሚደርሱ ከብቶች ይሞታሉ
* እንደተለመደው ኢህአዴግ የድርቅ አደጋና የምግብ እጥረት ስጋት የለም እያለ ነው ባለፉት ሁለት ወራት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተከሰተው የዝናብ እጥረት የድርቅ አደጋ እንዳይከሰት ስጋት የፈጠረ ሲሆን ግብርና ሚኒስቴር በበኩሉ፤ የዝናብ እጥረት ቢኖርም የድርቅ አደጋና የምግብ እጥረት ስጋት የለም ብሏል፡፡ በአፋር ክልል ግን ሁኔታው ተባብሷል፡፡ በየቀኑ እስከ 100 የሚደርሱ ከብቶች በመኖና በውሃ እጥረት እየሞቱ መሆኑን ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡ የአፋር ክልልን አቋርጠው ወደ ጅቡቲ ወደብ ከሚጓዙ ሹፌሮች አንዱ ለአዲስ አድማስ እንደገለፀው፤ በመንገድ ዳርና ዳር በርካታ በጎችና ፍየሎች ሞተው ይታያሉ፡፡ በክልሉ ካለፈው ዓመት ሰኔ ወር ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዝናብ የጣለባቸው ቀናት በጣት የሚቆጠሩ መሆናቸውን የጠቆሙት ምንጮች፤ የድርቁ ሁኔታ እየተባባሰ ቢሆንም በመንግስት … [Read more...] about በአፋር በየቀኑ እስከ 100 የሚደርሱ ከብቶች ይሞታሉ
የመድረክ አስቸኳይ ጉባዔ
በቅርቡ የተካሄደውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ሂደትና ውጤት እንደማይቀበለው ተቃዋሚው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት መድረክ ጉባዔ በይፋ አስታውቋል። “ኢሕአዴግ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ተመርጧል” የሚለው የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ አነጋገር አምባገነኖችን ያበረታታ ነው፤ ሲልም መድረክ ተችቷል። በሙስሊሙ ኅብረተሰብ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት፣ በሌሎች የሙስሊሙ ማኅበረሰብ አባላትና በጋዜጠኞች ላይ በቅርቡ የተላለፈውን ፍርድ ፍትሐዊ ያልሆነ፤ ኢሕአዴግ በሃይማኖታዊ ጉዳዮች ጣልቃ እንደሚገባ የሳየ ነው ብሏል መድረክ፡፡ ሰላማዊ ትግላቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ያስታወቁት የወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከሚቀጥለው ጉባዔው በኋላ መድረክ እንደሚዋሃድ ጠቁመዋል። ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል እዚህ ላይ ያዳምጡ፡፡ (ምንጭ፦ ቪ.ኦ.ኤ) … [Read more...] about የመድረክ አስቸኳይ ጉባዔ
የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር የባንክ ሒሳብ ውስጥ የተገኘው 675 ሚሊዮን ዶላር የማን ነው?
የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ነጂብ ራዛክ የግል የባንክ ሒሳብ ውስጥ 675 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ሆኖ ተገኘ፡፡ ይህም ገንዘብ ከየት እንደተገኘ የአገሪቱ የፀረ ሙስና ኮሚሽን በምርመራ እንዲያጣራ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተፅዕኖ እያደረጉ ናቸው፡፡ ኮሚሽኑ ባለፈው ሰኞ እንደገለጸው፣ 675 ሚሊዮን ዶላር ያህል ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ራዛክ የግል ሒሳብ ተዛውሯል፡፡ ይህም ገንዘብ በዕርዳታ የገባ እንጂ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሚመራው የአገሪቱ የኢንቨስትመንት ፈንድ የወጣ አለመሆኑን አመልክቷል፡፡ በአገሪቱ ውዝግብ ያስነሳውና የጠቅላይ ሚኒስትሩን መንግሥት ያንቀጠቀጠው ይኼ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ፣ በአገሪቱ ፀረ ሙስና ኮሚሽን በዕርዳታ የመጣ ነው ቢባልም፣ ኮሚሽኑ ዕርዳታውን የሰጠውንም ሆነ በባንክ አካውንቱ ያስቀመጠውን ግለሰብ ወይም አካል አላሳወቀም፡፡ በመሆኑም ኮሚሽኑ ሊያድበሰብስ … [Read more...] about የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር የባንክ ሒሳብ ውስጥ የተገኘው 675 ሚሊዮን ዶላር የማን ነው?
ኢህአዴግ በኤርትራ አራት አቅጣጫዎች ጥቃት ሊሰነዝር አስቧል
ኢህአዴግ በአራት አቅጣጫዎች የጦር ጥቃት ለመሰንዘር ማሰቡ ተሰማ፡፡ ይኸው ሃሳብ ለአሜሪካ ቀርቦላታል፡፡ በቅርቡ የተጠናከረ እንቅስቃሴ የጀመረው የአርበኞች ግንቦት ፯ ኃይል በተደጋጋሚ በሚያወጣው መረጃ በተለያዩ ቦታዎች ጥቃት ማድረሱን በይፋ ቢገልጽም ኢህአዴግ ጥቃቱን በቀጥታ ለማስተባበል እስካሁን አልወደደም። ይሁን እንጂ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ “ህዝብ አስፈቅደን” ሲሉ ኤርትራን እንደሚወጉ ይፋ አድርገዋል። አብዛኞች እንደሚስማሙበት ዛቻው ግጭት ስለመኖሩ የሚያረጋግጥ ነው። በሌላው አንጻር ደግሞ ይህንን የሃይለማርያም ንግግር የኤርትራው ሹም በዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የተለመደ የህወሃት/ኢህአዴግ ማስፈራሪያና ዛቻ በማለት አጣጥለውታል፡፡ የግጭቱን ደረጃና በኢህአዴግ ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን ኢሳት ይፋ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራን መውቀሰና ማስፈራራት የጀመረው ኢህአዴግ፣ … [Read more...] about ኢህአዴግ በኤርትራ አራት አቅጣጫዎች ጥቃት ሊሰነዝር አስቧል
ቴድሮስ አድሃኖም “ኢህአዴግ ቂመኛ አይደለም” አሉ
የኢህአዴግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም “ኢህአዴግ ቂመኛ አይደለም” ሲሉ ከቪኦኤ አማርኛው ክፍል ባልደረባ ትዝታ በላቸው ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አስታወቁ። ሚኒስትሩ ድርጅታቸውን ከደርግ ጋር በማነጻጸር ከቂም የጸዳ እንደሆነ ሲያስረዱ ጋዜጠኛዋ አማርኛ ተናጋሪዎች ላይ በቂም በቀል ስለተፈጸመውና እየተፈጸመ ስላለው ግፍ ጥያቄ አላቀረበችም። ሚኒስትሩ ኢህአዴግ በህግ የበላይነት ስለማመኑ በመረጃ አልተሞገቱም። በዘር፣ በብሄርና በጎሳ ላይ ተንጠልጥሎ ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ በስልጣን ላይ የቆየው ኢህአዴግ፣ በ፩፱፰፫ ስልጣን ከያዘ ጀምሮ በገሃድ አማርኛ ተናጋሪዎችን ከሌሎች ብሄረሰቦች ጋር በማናከስ፣ ቂም በማቋጠር፣ የስርአተ ማህበሮችን ችግሮች ከነፍጥ ጋር በማያያዝ እያላከከባቸው፣ “ነፍጠኛ” የሚል ስም በመስጠት የህዝብ ንብረት በሆነው መገናኛ የጥላቻ ዘመቻ በማራገብ … [Read more...] about ቴድሮስ አድሃኖም “ኢህአዴግ ቂመኛ አይደለም” አሉ
ኦባማ፡ “በንግግር (ወሬ) A፣ በተግባር D” ኦባንግ ሜቶ
ለፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ውጤት ቢሰጥ በእስካሁኑ የአፍሪካ ፖሊሲያቸው በንግግር (በወሬ) ደረጃ A በተግባር ግን D እንደሚሰጧቸው ኦባንግ ሜቶ አስታወቁ፡፡ አፍሪካውያንም ሆኑ ኢትዮጵያውያን ለነጻነት በሚያደርጉት ትግል ምዕራባውያን ዕንቅፋት ከመሆን እንዲቆጠቡ አስረዱ፡፡ በአሜሪካ ድምጽ የStraight Talk Africa አዘጋጅ ሻካ ሳሊ የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማን የአፍሪካ ጉብኝት በተመለከተ ከሁለት ቀናት በፊት ባዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ሦስት አፍሪካውያንን ተጋብዘው ነበር፡፡ ከሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ የሴራሊዮኑ ፕሮፌሰር አብዱል ካሪም ባንጉራ፣ የአፍሪካ ስደተኞች ስብስብ ኃላፊ ጋናዊው ኒ አኩቴ እና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር ኢትዮጵያዊው ኦባንግ ሜቶ ነበሩ፡፡ በእስካሁኑ የአፍሪካ ፖሊሲያቸው ለፕሬዚዳንቱ ምን ውጤት ትሰጣላችሁ በማለት ሻካ ላቀረበው ጥያቄ ዶ/ር አብዱል D … [Read more...] about ኦባማ፡ “በንግግር (ወሬ) A፣ በተግባር D” ኦባንግ ሜቶ
ብርሃኑ ነጋ “… ዱር ወጡ …”
* የሠራዊቱ ሞራል ከፍ ብሏል ከአርበኞች ግንባር ጋር የተዋሃደው የግንቦት ሰባት ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋና የፓርቲው የአመራር አባላት የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ታጣቂዎቻቸው ወደሚንቀሣቀሱባት ኤርትራ ጠቅልለው መሄዳቸውን የአመራር አባላቱ አስታወቁ፡፡ ብርሃኑ አስመራ መግባታቸው ከተሰማ በኋላ የሠራዊቱ ሞራል ከፍ ማለቱና ከአገር ውስጥ ግምባሩን ለመቀላቀል የሚፈልገው ሕዝብ እየጨመረ መምጣቱ ይነገራል፡፡ ቁጥራቸው ይፋ ያልተደረገ የአርበኞች ግንቦት ሰባት የአመራር አባላትን ይዘው ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ ኤርትራ ያመሩት ሌሎች አማራጮችን ጨምሮ በብረት ትግልና በሕዝባዊ ንቅናቄ የኢትዮጵያን ገዥ ፓርቲ ለማስወገድ መሆኑን የአመራር አባላቱ ይናገራሉ፡፡ “ዶ/ር ብርሃኑ ነጋና ጓዶቻቸው ትግል ወደሚካሄድባቸው አባባቢዎች ያመራሉ” ሲሉ የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራር አባል ዶ/ር ታደሰ ብሩ … [Read more...] about ብርሃኑ ነጋ “… ዱር ወጡ …”