የሳውዲ ባለሃብቶች እነሱ “የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት” ያሏቸው አንዳንድ የህወሃት/ኢህአዴግ ሹሞች መሬታቸውንና መሣሪያዎቻቸውን የዘረፏቸው መሆኑን በማስታወቅ ክስ አሰሙ፡፡ ህዳር 15 ቀን 2008 ዓም በወጣው ታዋቂው የሳውዲ ጋዜጣ አረብ ኒውስ በኢትዮጵያ ባለው አገዛዝ አንዳንድ ባለሥልጣኖች መሬታቸውን እየተቀሙ በደልና ዘረፋ እየተፈጸመባቸው መሆኑን በአፍሪካ የሳውዲ ባለሃብቶችን ቡድን የሚመሩት ሞሀመድ አልሸህሪ የተባሉ ባለሃብት ለአረብ ኒውስ አስታውቀዋል። እኒሁ ባለሃብቶችን መርተው ወደ አፍሪካና ወደ ኢትዮጵያ ከአመታት በፊት ወደ የዘለቁት ባለሃብት አንዳንድ የአገዛዙ ኃላፊዎች በኢንቨስትመንት ፈቃድ ወደ ሀገሪቱ ያስገቡትን ንብረቶች ለመውረስ በእርሳቸውና በጓደኞቻቸው ላይ የወንጀል ክስ እንደተመሰረተባቸው ማስታወቃቸውን አረብ ኒውስ ዘግቧል። ቅሬታ አቅራቢው ሳውዲ ባለሃብት ሞሃመድ አልሸህሪ … [Read more...] about በህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ባለሥልጣናት “ተዘርፈናል” – የሳውዲ ባለሃብቶች!
News
ዜና
ከ9ሺህ በላይ ፈላሻ ሙራዎች ወደ እስራኤል ሊጓዙ ነው
ከ25 ዓመታት በላይ ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል ለመጓዝ እየጠበቁ ያሉ በተለየ ፈላሻ ሙራ ተብለው የሚጠሩት ቤተ እስኤላውያን ወደ “ቅድስት አገራቸው” እንዲመጡ የእስራኤል መንግሥት ወሰነ፡፡ እስኤል እንደገቡም የአይሁድ እምነትን በተመለከተ የተሃድሶ ትምህርት እንደሚሰጣቸው ተመልክቷል፡፡ በእስራኤል ያሉ እና ሌሎች ዓለምአቀፋዊ የዜና ምንጮች እንደዘገቡት የጠ/ሚ/ር ቢኒያም ኔታንያሁ መንግሥት ውሳኔውን ያስተላለፈው እሁድ ዕለት በሙሉ ድምጽ ነበር፡፡ ይህ የአሁኑ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት የዛሬ ሁለት ዓመት እስራኤል ምንም ዓይነት ዜጋዋ በኢትዮጵያ እንደሌለ ይፋ ነበር፡፡ “ዛሬ ጠቃሚ ውሳኔ አስተላልፈናል” በማለት የተናገሩት ኔታንያሁ ውሳኔው በእስራኤል እየኖሩ ከቤተሰቦቻቸው ለተለያዩት ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሰጪና ጠቃሚ እንደሆነ በላኩት መግለጫ አመልክተዋል፡፡ ከዚህ በፊት እስራኤል “የተስፋዋ … [Read more...] about ከ9ሺህ በላይ ፈላሻ ሙራዎች ወደ እስራኤል ሊጓዙ ነው
ለድርቁ አስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል ይቋቋም!
* ከአገዛዝ ለውጥ በፊት ችጋር ይቀድማል? * “በአሁኑ ጊዜ ችጋሩ እንደ 1977 ሆኗል!” በኢትዮጵያ ላለፉት ፴ ዓመታት ያለታየ ችጋር ተከስቷል። ድርቁና ረሃቡ ከዚህም በላይ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ኢህአዴግን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት ይፋ እያደረጉ ነው። “የምግብ ዋስትናን አረጋግጫለሁ” በማለት ሲወተውት የኖረው ህወሃት ተገዶ ያመነው ችጋር ከ፩፱፯፯ ድርቅ በላይ የከፋ እንደሚሆን ስጋት አይሏል። ከዚህ በፊት እንደተከሰቱት ለውጦች ይህኛውም የአገዛዝ ለውጥ ሊያስከትል እንደሚችል ተነገረ። በአስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል መቋቋም እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ ህወሃት ከድርቅ እና ድርቅን ተከትሎ ከሚገኝ ዕርዳታ ጋር በተያያዘ ካለው አስጸያፊ ተሞክሮ በመነሳት ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንደሚሉት ከድርቁ ጋር በተያያዘ ፍትሐዊነት ያሳስባቸዋል፡፡ ሲያብራሩም በከፍተኛ የሙስና እና የአድልዖ … [Read more...] about ለድርቁ አስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል ይቋቋም!
“ዘመድነህ ንጋቱ የኩባንያው ሳይሆን የህወሃት አገልጋይ ናቸው”
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በሚገዛት ኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ስም የኧርነስትና ያንግ የተሰኘውን የንግድ ሒሳብና ኦዲት ሥራ የሚያከናውን ኩባንያ ከፍተው በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት ዘመድነህ ንጋቱ በኦባንግ ሜቶ ለዓምአቀፉ የኧርነስትና ያንግ ኩባንያ የሥራ ኃላፊዎች አቤቱታ ቀረበባቸው፡፡ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ለዓለምአቀፉ የኧርነስትና ያንግ ኩባንያ ዋና የሥራ ኃላፊዎች ማርክ ዋይንበርገር እና ሮጀር ደንባር ጥቅምት 9፤2008 ዓም (October 20, 2015) በጻፉት ደብዳቤ የኩባንያው ሸሪክ አስተዳዳሪ አቶ ዘመድነህ ንጋቱ ኩባንያው ከቆመለት ዓላማ ውጪ በመንቀሳቀስ ከህወሃት ጋር በማበር ከሙያው ሥነምግባር ያፈነገጠ አካሄድ በመሄድ የኢትዮጵያ ሕዝብ እየበደሉ መሆናቸውን አውስተዋል፡፡ “ላለፉት 14 ዓመታት” ይላል ደብዳቤው … [Read more...] about “ዘመድነህ ንጋቱ የኩባንያው ሳይሆን የህወሃት አገልጋይ ናቸው”
ሠራተኛውን ማን አቃጠለው?
የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) ከጥቂት ቀናት በፊት በአፋር ክልል ሃዳር ወረዳ ኤሊ ውሃ ከተማ ቅዳሜ መስከረም 22፤2008 ዓም ስለተፈጸመው ግድያ መረጃ ልከውልናል፡፡ ከመረጃ አቀባያችን ጋር በተደጋጋሚ በተላላክነውና ባቀረብነው በርካታ ጥያቄዎች መሠረት ያገኘነው መረጃ ይህንን ይመስላል፡- እጅግ ዘግናኝ የሚባለው ግድያ የተፈጸመው ከላይ በተጠቀሰው ሥፍራ በሚገኘው የቻይና መንገድ ሥራ ፕሮጀክት እየተባለ በሚጠራው ግቢ ውስጥ ነው፡፡ የእማኝ ዘጋቢው በራሳቸው አገላለጽ እንዲህ ዘግበውታል፡- (የላኩልን የእንግሊዝኛ ፊደላትን በመጠቀም ሲሆን ወዳማርኛው እንዲህ መልሰነዋል) “ወንጀሉ የተፈጸመው ቅዳሜ መስከረም 22፤2008 ዓም በአፋር ክልል ሃዳር ወረዳ በኤሊውሃ ከተማ ግቢ ተብሎ በሚጠራው የቻይና መንገድ ሥራ ፕሮጀክት ውስጥ ነው፡፡ የተቃጠለው ልጅ ወልዱ ይባላል፡፡ በ(ፕሮጀክቱ) … [Read more...] about ሠራተኛውን ማን አቃጠለው?
ነጻ አውጪ ግምባር አገዛዝ እንጂ መንግሥት አይመሠርትም
ላለፉት 25 ዓመታት በነጻ አውጪ ግምባር ስም ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር "ኢህአዴግ" ብሎ በፈጠረው ስያሜ አገር በግፍ እየገዛ መሆኑ ሳያንስ በየአምስት አመቱ በሚያካሂደው "ምርጫ" የሚመሠርተው "መንግሥት" መፍትሔ ሊሰጥ እንደማይችል መድረክ አስታወቀ። ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ በኢትዮጵያ ለተከሰተው ረሃብ የአገዛዙ ፓርቲ ተጠያቂ ነው ይላል። የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ "ኢህአዴግ ያቋቋመው መንግስት መፍትሄ አይሰጥም ተባለ" በሚል ርዕስ ያወጣው ዜና ከዚህ እንደሚከተው ይነበባል:- ኢትዮጵያ ውስጥ እየተስተዋለ ያለው ረሃብ የገዥው ፓርቲን ፖሊሲ ውድቀት ያሳያል ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ከሰሰ፡፡ ኢህአዴግ ያቋቋመዉ አምባገነን መንግስት ለኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግሮች መፍትሄ ሊሰጥ አይችልም ሲል ታቃዋሚዉ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ … [Read more...] about ነጻ አውጪ ግምባር አገዛዝ እንጂ መንግሥት አይመሠርትም
ቅጥ ላጣው ሙስና “ተጠያቂ ነኝ” – ህወሃት
ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር - ህወሃት በተለይ በአዲስ አበባ ቅጥ ያጣውን ሙስናና ዘረፋ በተመለከተ በጠራው ስብሰባ አስቀድሞ በመቀሌው "ተጠያቂ ነኝ" በማለት እንዳመነው አሁን ደግሞ ነዋሪው ችግሩን ራሱ እንዳመጣው ራሱ ይፍታው ማለቱ ተነግሮዋል:: የሪፖርተር ዘገባ እነሆ:- * ሙስና በአዲስ አበባ በኔትወርክ ተይዞዋል ሙስና፣ ኪራይ ሰብሳቢነትና የመልካም አስተዳደር እጦት ከወረዳ እስከ ከተማ አስተዳደሩ ድረስ በኔትወርክ የተያያዙ በመሆናቸው ሊፈታቸውም ሆነ ሊያስቆማቸው የሚችለው ድርጅቱ ኢሕአዴግ ብቻ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን መስከረም 20 ቀን 2008 ዓ.ም. በግዮን ሆቴል ለግማሽ ቀን አዘጋጅቶት በነበረው የውይይት መድረክ ላይ ከተለያዩ የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ የሁሉም ክፍላተ ከተሞች፣ … [Read more...] about ቅጥ ላጣው ሙስና “ተጠያቂ ነኝ” – ህወሃት
የሐጃጆች ሞት
ለሐጅ ጉብኝት የተጓዙ በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ምዕመናን ትናንት ሚና-ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ ድንገት በመሞታቸዉ የሐገራት መሪዎችና የድርጅት ተጠሪዎች የሚያስተላልፉት የሐዘን መግለጫ፤ የሐይማኖት መሪዎች ፀሎት ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ። በአደጋዉ 717 ሰዎች ሞተዋል፤ ከ800 በላይ ቆስለዋል። የሳዑዲ አረቢያ ገዢዎች የአደጋዉ ትክክለኛ መንሥኤ እንዲጣራ አዘዋል።ኢራን ግን ለአደጋዉ የሪያድ ነገሥታት ሐላፊነቱን እንዲወስዱ አሳስባለች።በሐጂ ጉብኝት ወቅት ተደጋጋሚ አደጋዎች ቢደርሱም በርካታ ሠዉ የሞተበት አደጋ ሲደርስ በሃያ-አምስት ዓመት ዉስጥ የትናንቱ የመጀመሪያዉ ነዉ። ከመካዉ ዓል-ሐራም እስከ ሞስኮዉ ካቴድራል፤ ከምሥራቅ ለንደኑ እስከ ካይሮዉ አል-አዝሐር፤ ከካምፓላዉ ቃዛፊ፤ እስከ እየሩሳሌሙ ዓል-አቅሳ፤ ከዓለም መሳጂዶች የሚንቆረቆረዉ ዱዓ፤ምልጃ ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ።ከዋይት ሐዉስ እስከ … [Read more...] about የሐጃጆች ሞት
ህወሃት ጦርነት ጀመረ፣ ቁስለኞች ታይተዋል
በነጻ አውጪ ስም አገር እየገዛ ያለውን የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃትን) ለመውጋት ብረት ያነሳው ሌላ የትግራይ ነጻ አውጪ ሃይል /ትህዴን ወይም በትግሪኛ ዴምህት/ መሪ የነበረው “ተጋዳላይ” ሞላ አስገዶም ህወሃትን ከተቀላቀለ ጥቂት ቀናት በኋላ ጦርነት መጀመሩ ተሰማ። የህወሃት ወኪል ሃይለማርያም ደሳለኝ ውጊያው የሚጀመረው የህዝብ ፈቃድ ተጠይቆ እንደሚሆን ተናግረው ነበር። የጎልጉል መረጃ አቀባዮች ከአዲስ አበባ እንደገለጹት ጦር ኃይሎች ሆስፒታል ቁስለኞች እየገቡ መሆኑንን እማኞች ነግረዋቸዋል። ጦርነቱ በየትኛው መንደርና ወረዳ እንደተጀመረ ለይተው ያላስረዱት የዜናው ባለቤቶች፣ ውጊያ እየተካሄደ ያለው ኤርትራ ምድር ላይ እንደሆነ ግን አልሸሸጉም። አንድ የሆስፒታል ሰራተኛ ዘመድ ደውሎላቸው “ቁሰለኞች አሉ ሥራ በዝቶብኛል” ማለታቸውን የጎልጉል መረጃ ሰጪዎች ከአዲሰ አበባ … [Read more...] about ህወሃት ጦርነት ጀመረ፣ ቁስለኞች ታይተዋል
ክላሽንኮቭ ያነገበ የህወሃት ታጣቂ የወጣቷን ህይወት አጠፋ
አንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል ለቡ አካባቢ በሚገኝ መዝናኛ ቤት ውስጥ ሰኞ ምሽት አንዲት ወጣት መግደሉ ተሰማ፡፡ ግለሰቡ ራሱን ለማጥፋት ቢሞክርም ተርፎ በሕክምና ላይ ይገኛል፡፡ ሰሎሜ ጉልላት የተባለችው የ20 ዓመት ወጣት ከጓደኛዋ ጋር በመሆን በለቡ ኮንዶሚኒየም ቤቶች አካባቢ በሚገኝ የጓደኛቸው መዝናኛ ውስጥ በመዝናናት ላይ እያሉ ነው ከተጠርጣሪው ገዳይ ጋር የተገናኙት፡፡ ለጊዜው ስሟን መናገር ካልፈለገችው ጓደኛዋ መረዳት እንደተቻለው፣ የፖሊስ የደንብ ልብስ የለበሰው ግለሰብ ከዚህ ቀደም ሰሎሜን አስቸግሮ ከሚያውቅ ግለሰብ ጋር በሚዝናኑበት ባር ውስጥ እንደነበር ትናገራለች፡፡ ሁለቱ ሴት ጓደኛሞች መዝናኛ ባሩ ውስጥ የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀው ከመውጣታቸው በፊት፣ ወደ መፀዳጃ ቤት ለመግባት ተስማምተው መሄዳቸውን ታስታውሳለች፡፡ ክፍሉ ራሱን የቻለ መዝጊያ ኖሮት መፀዳጃ ክፍሎቹም … [Read more...] about ክላሽንኮቭ ያነገበ የህወሃት ታጣቂ የወጣቷን ህይወት አጠፋ