• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል!

March 2, 2020 11:24 am by Editor 1 Comment

ስለ ዓድዋ ጦርነት አንዳንድ እውነታዎች❗️

ቀን: የካቲት 23, 1888
ቦታ: አድዋ፤ ኢትዮጵያ
አሸናፊው ሀይል: ኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ በኩል የነበሩ የጦር አዛዦች
አጤ ምኒልክ
እቴጌ ጣይቱ
ተክለ ሀይማኖት
ራስ መኮንን
ራስ ሚካኤል
ራስ መንገሻ
ፊታውራሪ ገበየሁ
ፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ
ፊታውራሪ ዳምጠው
ደጃዝማች ባልቻ ሳፎ
ኒኮላ ሊዮንቴቭ

በጣልያን በኩል የነበሩ የጦር አዛዦች
ኦሬስቴ ባራቴሪ
ቪቶሪዮ ዳቦርሚዳ
ጁሴፔ አሪሞንዲ
ማቲዎ አልቤርቶኒ
ጁሴፔ ኤሊና

በኢትዮጵያ በኩል የተሰለፈ የጦር ብዛት
80,0000 መሳርያ የታጠቅ
20,000 ጦርና ጎራዴ የታጠቀ
8,600 ፈረሰኛ

በጣልያን በኩል የተሰለፈ የጦር ብዛት
24,804 ዘመናዊ መሳርያ የታጠቅ ወታደር
56 ረጅም ርቀት ተወርዋሪ መሳርያዎች

በኢትዮጵያ በኩል የተሰዉ ጦረኞች ቁጥር
3867 የሞቱ
ከ8000 በላይ የቆሰሉ

በጣልያን በኩል የተሰዉ ጦረኞች ቁጥር
6394 የሞቱ
1428 የቆሰሉ
ከ3000 በላይ የተማረኩ

© መልካም 74 Radio

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    March 2, 2020 04:09 pm at 4:09 pm

    የዛሬን አያርገውና የአድዋ ድል ለመላው ጥቁር ህዝብ የድል ጮራ እንደሆነ በየትምህርት ቤቱ እንማር ነበር። አስታውሳለሁ አንድ ጊዜ በአንድ ትምህርት ቤት ግርማ ፍስሃ የተባለ የጀርመን ኗሪ አባቱን ሊጠይቅ ብቅ ይላል። ጊዜው ክረምት ነበረ። እኛም ተማሪዎች የክረትም ትምህርት እንድንማር (ሃገርህን እወቅ) አይነት ነገር ደ/ች መንገሻ ይልማ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ተኮልኩለናል። ሰብሰብ ብለን በኦሮምኛ እየዘፈንን ስንቀላለድ ደወል ተደወለና ገባን። በቀኑ ግርማ ፍስሃ ተጋባዥ አስተማሪ ነበር። ሰላም ልጆች በማለት ራሱ ካስተዋወቀ በህዋላ ለዛሬ የማስተምራችሁ “አርሙኝ” ከተሰኘ መጽሃፍ ውስጥ ” አልሞትም ብዬ አልዋሽም የተሰኘውን ታሪክ በማንበብ እጀምራለሁ በማለት የአቶ ተማቹንና የወ/ሮ ጽጌረዳን በጣሊያን ወረራ ጀግንነት ማንበብ ጀመረ። በማህሉ ሲቃ ያዘውና ማልቀስ ጀመረ። ክፍሉም ሁሉ አብሮት አለቀሰ። ያ ጊዜ እንደ አሁኑ በዘር ዙሪያ ሰው ያልተሰፈረበት ሁሉም በሰላምና በህብረት የሚኖርበት የመልክዓ ምድር የመማሪያ መጽሃፋችን አርዕስት “አብሮ መኖር በዓለም ዙሪይ” የሚል እንደነበር ትውስ ይለኛል።
    ወደ ዛሬው የዘር ፓለቲካ ስንመለስ ደግሞ ሌቦች ጀግና የሚባሉበት፤ ወንድም እና እህቱን ገድሎ ሰው የሚፎክርበት፤ ለዘሬ፤ ለጎሳዬ፤ ለክልሌ በማለት ሰው ሁሉ በየጎራው የሚፎልልባት፤ በብሄር ነጻነት ስም ባርነት ውስጥ የምንኖርበት በጥቅሉ የደንበር ገተር ጊዜ ላይ እንገኛለን። አድዋ ከሃገሪቱ አራት ማዕዘናት ሃበሾች ተጠራርተው ጠላትን ያሳፈሩበት የድል ጎራ ናት። የአድዋው ድል የጋራ ድል ነበር ነውም። ሼሁ ከመስጊድ፤ ቄሲ ከመንበሩ፤ ገበሬው ከእርሻው፤ ነጋዴውና ሌላውም ተጠራርተው የነጭ መንጋን ያሳፈሩበት የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ጮራ! ታሪክን ሰርተው በታሪክ ውስጥ ያለፉ ጀግኖች ደምና አጥንት ዛሬም በአድዋ ሸለቆና ተራራዎች ይጣራል፤ ይናገራል። የሚሰማ ግን የለም። የክልል ፓለቲካ ያሰከረው የእብድ ክምችት ያፈራች ሃገር። ሲያሳዝን! በአዲስ አበባ ለሰላም ገቡ የተባሉ ጠበንጃ አንጋችና አፋዊ ፓለቲከኞች በለመድት የፓለቲካ የሾኬ ጠለፋ ሰውን ያተራምሳሉ። መማር ማለት እንዲህ ነው። ነጻ እናወጣሃለን የሚባለውን ሰው እሳት ውስጥ እየገፉ መክተት። ዶ/ር አብይም እየቆ መንግሥቱንና አቶ መለስን ለመምሰል ጥቂት ጊዜ የቀረው ይመስላል። በቅርቡ ከብዙ ውጣ ውረድ በህዋላ አንድ የደረስኩበትን መረጃ አልባ የሆነ የራሴን አስተያየት ልስጥ። ሁልጊዜ ኢንጂኒየር ስመኘውን ማን ገደለው በማለት እጠይቅ ነበር። መልሱ ጠ/ሚሩ ናቸው። እንዴት ለሚል። ባፋቸው። ግድቡን በጊዜው ሄደው ከጎበኙ በህዋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እጠቅሳለሁ ” ግድቡ በአስር ዓመት ጊዜም አያልቅ” ይህ ይፋዊና ፌዚያዊ ንግግር ኢንጂኒየሩን ጎድቶታል። በዚህም የተነሳ ራሱን ለማጥፋት ተገዷል። የእኔ ድምዳሜ እሱ ነው። አብይ የማያውቀው የእውቀት ሚዛን የለም። መለፍለፍ ልምድ አድርጎታል። ቃልም ተግባርም በሚዛን ሲሆን መልካም ነው። እንዲሁ ራስን እንደ (chameleon ) ከከባቢ ጋር እየለዋወጡ ቢዘላብድት ዋጋ የለውም። የሚገርመኝ ነገር ባለስልጣኖች እየቆዪ የንጉስ አይነት መልክና ባህሪን ይላበሳሉ። መታመም ነው። ንጉስ ድሮ ቀረ። ይህን አስቀድመው ያዪት እውቁ የወረሂመኖው ሸህ ሁሴን ጅብሪል እንዲህ ብለው ነበር።
    ያምናን ቀን አማሁት ላፌ ለከት የለው፤
    የዘንድሮው መጣ እጅ እግር የሌለው፤
    ቀን ይወጣል ብየ ብጠብቅ ባስጠብቅ፤
    እንኳን ቀን ሊወጣ ጨለማ ነው ጥቅጥቅ፡፡
    ይህ ግጥም የሚያሳየው ትሻልን ትቼ ትብስን እንዲሉ አይነት ነው። ብቻ የጋራ የሆነ ድላችንን እያንቋሸሽን የአንድ ቀን አውሎ ንፋስ የሚደረምሰውን የክልልና የቋንቋ አጥር ስንገነባ ኖረናል ተብለን አፈር ይመለስብናል። አታድርስ ነው። ድንበር ተሻጋሪ ሥራ ከመስራት ላስን አጥቦና አሳንሶ መሞት! እንትፍ ይቅርብኝ!
    አድዋ የጀግኖች የድል ሥፍራ። አድዋ የብዙሃን መቃብር ቦታ። አድዋ የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ጮራ። ኑሪ ለዘላለም ለህያዋን ተስፋ ለወደቁልሽ ሰማእታት የክብር ሥፍራ!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule