• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቤተልሔም ፕላዛና ደብረወርቅ ታወር አገልግሎት እንዳይሠጡ ተከለከሉ

July 17, 2013 09:22 am by Editor 2 Comments

(ከጎልጉል አዘጋጅ – ለመስታወቱ ብቻ ቤተልሔም 9ሚሊዮን ብር ደብረወርቅ ደግሞ ከ15ሚሊዮን ብር በላይ አውጥተው እዚህ እስኪደርስ ድረስ የከንቲባ ኩማ መስተዳድር የት ነበር? ላዲሱ ከንቲባ ድሪባ የከተማውን ቁልፍ ሲያስረክብ ይሆን?)

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አገልግሎት መስጠት ከጀመሩ ከሁለት ዓመት በላይ የሆናቸው ሁለት ሕንፃዎች ደረጃቸውን deribaአልጠበቁም በሚል ምክንያት የመጠቀሚያ ፈቃድ ከለከላቸው፡፡ሁለቱ ሕንፃዎች መገናኛ ድልድይ አካባቢ የሚገኘው ቤተልሔም ፕላዛና ሜክሲኮ አካባቢ ከቡናና ሻይ ሕንፃ ፊት ለፊት የሚገኘው ደብረ ወርቅ ታወር ናቸው፡፡

ሁለቱ ሕንፃዎች የተጠቀሙበት የውጭ መስታወት አንፀባራቂ ነው በሚል ምክንያት አስተዳደሩ መስታወታቸው እንዲነሳ ማዘዙ ታውቋል፡፡

መገናኛ የሚገኘው ቤተልሔም ፕላዛ ባለ ሰባት ፎቅ ነው፡፡ ያረፈው በ800 ካሬ ሜትር ቦታ ነው፡፡ ለግንባታው በአጠቃላይ 40 ሚሊዮን ብር መውጣቱን፣ ለመስታወቱ ብቻ ዘጠኝ ሚሊዮን ብር ወጪ እንደተደረገ ከሕንፃው አስተዳደር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ሕንፃው ከሦስት ዓመት በፊት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን፣ በርካታ የንግድ ተቋማት እስከ አንድ ዓመት ድረስ ለመቆየት የኪራይ ውል ፈጽመው ሥራቸውን እያከናወኑበት ነው፡፡

አስተዳደሩ ያሳለፈው ውሳኔ ተግባራዊ የሚሆን ከሆነ ተከራዮቹ ለቀው እንደ አዲስ የመስታወት ነቀላና ተከላ መካሄድ ይኖርበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የሕንፃው ባለቤት የጣፋጭ ቤተልሔም ባለቤት አቶ ነጋሽ ባልቻ ናቸው፡፡

የደብረ ወርቅ ታወርም ይኸው ውሳኔ ተግባራዊ እንደሚሆንበት ተነግሯል፡፡ ደብረ ወርቅ ታወር ከፍታው 13 ፎቅ ሲሆን፣ ለወርቃማው መስታወት ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ እንደወጣ ይነገራል፡፡

ደብረ ወርቅ ታወር በ500 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ሕንፃ ሲሆን፣ ለሕንፃው የወጣው ወጪ ተሰልቶ እንዳለቀ ባለቤቱ አቶ ተመስገንን ከፍያለው ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የሁለቱ ሕንፃዎች ባለቤቶች የአስተዳደሩን ውሳኔ አልተቀበሉትም፡፡ ምክንያታቸውም ሕንፃዎቹ የተገነቡት በግልጽ እየታየ ነው፡፡

ከተከራዮች ጋር ውል ገብተው ከሁለት ዓመታት በላይ አገልግሎት ከሰጡ በኋላ እንዲህ ዓይነት ውሳኔ መወሰኑ አግባብ አለመሆኑን በመጥቀስ መከራከራቸውን ቀጥለዋል፡፡ አቶ ተመስገን እንዳሉት፣ ሕንፃቸው ወርቃማ ቀለም እንዲኖረው ያደረጉት ለውበት ብለው ነው፡፡ በዚያ ላይ ደረጃውን የጠበቀና ድርብ በመሆኑ ሙቀት የለውም፣ አያንፀባርቅም ይላሉ፡፡

የሊዝ አዋጅና የሕንፃ አዋጅ በሕንፃ የመጠቀሚያ መስፈርትን በሚመለከት ድንጋጌ አውጥተዋል፡፡ ማንኛውም ሕንፃ በዲዛይኑ መሠረት ተገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ ሲሆን በሕንፃ የመጠቀም ፈቃድ ጠይቆ ሲያገኝ አገልግሎት መስጠት ይችላል፡፡ ነገር ግን እነዚህ አዋጆች ሕንፃዎች ማሟላት ስለሚኖርባቸው ቁም ነገሮች የሚናገሩ ቢሆኑም፣ ይህ አሠራር ብዙም ተግባራዊ ሳይሆን ቆይቷል፡፡

እነዚህ ሁለት ሕንፃዎች የድንጋጌዎቹ የመጀመሪያ ሰለባዎች ሆነዋል፡፡ እነዚህ ሕንፃዎች በአንፀባራቂነት ቢፈረጁም በከተማው ውስጥ በርካታ ሕንፃዎች በዲዛይናቸው ለፓርኪንግ የተተወውን ቦታ ለሱፐር ማርኬትና ለመሳሰሉት ሥራዎች እያዋሉ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተጨማሪም በዲዛይኑ ላይ የሌሉ ተቀጥላዎችንም እንደሚጨምሩ ይስተዋላል፡፡

አስተዳደሩ በቀጣይነት በእነዚህ መሰል ግንባታዎች ላይ ፊቱን እንደሚያዞር መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ (ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    July 17, 2013 08:40 pm at 8:40 pm

    Are they owned by hodam Amharas who did not properly weep when Fascist Meles Zenawi died? or hodam Amharas/Oromos/Guraghies etc who did not pay enough Money for woyane Grand theft Programme called – DAM

    Reply
    • selam says

      July 19, 2013 01:59 pm at 1:59 pm

      Ante qoshasha Erterawi neh what ur trying is an old Game so its over try some thing ealse u b$%# hodam malet ertrians nach edemi lekachewon ethiopian lemebelat afachew wuha moleto eyalegegu 21amet beqezzet yasalefu so menem yehun men it is not ur f….ing problem diqala.

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule