• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በማር በበርበሬ በጤፍና በቅቤ ምርት ላይ ለጤና ጠንቅ የሆኑ ባዕድ ነገሮች የቀላቀሉ ተያዙ

September 3, 2021 01:54 pm by Editor Leave a Comment

በደቡብ ክልል በማር፣ በበርበሬ፣ በጤፍና በቅቤ ምርት ላይ ለጤና ጠንቅ የሆኑ ባዕድ ነገሮች ተቀላቅሎ ሲዘጋጅ መያዙን የደቡብ ክልል ንግድ ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ  ከፋ ዞን፣ ቦንጋ ፣ጌዴኦ ዞን ፣ዲላና  ሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተሞች ላይ ባደረገው የዳሰሳ ጥናት በማር ፤በበርበሬ በጤፍና በቅቤ ምርቶች  ላይ ለጤና ጠንቅ የሆኑ ባዕድ ነገሮች ተቀላቅሎ ሲዘጋጅ መያዙን የደቡብ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ  ምክትል ኃላፊ አቶ ሽመልስ ዋንጎሬ ተናግረዋል።

የጥራት ደረጃቸውን  ያልጠበቁ  የምግብ ምርቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከቱና እየተላመዱ መምጣታቸውን  በተደረገው የዳሰሳ ጥናት መረዳት ችለናል ያሉት ኃላፊው ህብረተሰቡ ምግብና ምግብ ነክ የሆኑ ነገሮችን ሲሸምት አጢኖ ሊሆን እደሚገባም አሳስበዋል።

ፎሼ የተሰኘ የጥራት ደረጃውን ያልጠበቀ ለምግብነት የማይሆን  በርበሬ ከእርድና ከስንደዶ ማቅለሚያ ኬሚካል ጋር በመደባለቅ ፤ማርን ከሞላሲስ ፣ቅቤን ከጄሶ፣ከአትክልት ተዋፅኦና የእንሰት ምርት ከሆነው ቡላ ጋር እንዲሁም ጤፍን ከካሳቫ ጋር ተከልሶ ለገበያ ሲቀርብ መያዙንም ኃላፊው አረጋግጠዋል።

የደቡብ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን በበኩላቸው መጪው ጊዜ በዓል ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ግብይት የሚፈፀም በመሆኑ ሸማቹ ህብረተሰብ ለጤና ጎጂ የሆነ ባዕድ ነገር የተቀላቀለባቸውን የምግብ ምርቶች ሲሸምት በጥንቃቄ ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል። (ኢብኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Right Column, Social

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule