ቒጫ የጉራግኛ ቃል ሲሆን ጥሬ ትርጉሙም ደንብ፣ ስርዓት፣ ህግ ማለት ነው፡፡ የጉራጌ ህዝብ ባህላዊ ስርዓት ህግ ራሱን በራሱ መገልገል የጀመረው በስሙ እየተጠራ ባለበት ሀገር ከሰፈረበት ዘመን ጀምሮ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ይሁን እንጂ ህብረተሰቡ በየክፍሉ የሸንጎ ማእከላት በክፍለ ህዘብ ምድብ ባለበት ሁሉ የስሙ አሰያየሙ ይለያያል፡፡ መደበኛ ህግ ክፍሎች አሉት፡፡ የፍትሃብሄር፣ ወንጀለኛና የቤተሰብ (የጋብቻ) ስነስርዓት (ህግጋት) በውስጡ ይዟል፡፡ ይኽውም፡- የአንቂት ቒጫ - ይህ ደንብ በአጠቃላይ የጋብቻና የፍቺ ስነስርዓት የተደነገገበት ሲሆን የአተጫጨት፣ የቸግ ወይም የኒካ የሰርግ እና ፍቺ አፈጻጸም የሚዳኝበት ስርዓት (ደንብ) ነው፡፡የቅየ ቒጫ - ይህ ደንብ በሁለት ወሰንተኞች መካከል የድንበር መገፋፋት እንዳይኖር በሁለት ወገኞች ስምምነት በሚመረጡ ሽማግሌዎች አማካይነት … [Read more...] about የጆካ ዳኞች ባህላዊ የዳኝነት ሥነ-ሥርዓት
Religion
ሃይማኖታዊ
የኢሬቻ በዓልን ለመረበሽ የተዘጋጁ 503 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
መስከረም 23 እና 24 የሚከበረውን የኢሬቻ በአል ለመበጥበጥ የተዘጋጁ 503 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ መሳሪያም ተገኝቶባቸዋል። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ኮማንደር አራርሳ መርዳሳ ትላንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለፁት፤ የኢሬቻ በዓል ላይ የሚሳተፉ የበዓሉ ታዳሚዎች በሰላም ወጥተው እንዲገቡ ኮሚሽኑ በጥብቅ እየሰራ ነው። የግል ፍላጎታቸውን ለማሳካት በተለያየ አቅጣጫ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ሀይሎች እንዳሉና ኮሚሽኑም እንደደረሰባቸው የገለፁት ኮማንደሩ፤ እስካሁን ድረስ 503 ሰዎች፣14 ክላሽ ፣ 26 ቦምብ እና 103 ሽጉጦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል፡፡ ከኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው የኢሬቻ በዓል በኮረና ምክንያት እንደ ከዚህ ቀደሙ በርከት ባለ ሰው የማይከበር ሲሆን በገዳ … [Read more...] about የኢሬቻ በዓልን ለመረበሽ የተዘጋጁ 503 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
ኦሮሞዎች በየዓመቱ ለሚያከብሩት ኢሬቻ በዓል ቦታ ተሰጠ
የኦሮሞ ተወላጆች በየዓመቱ ለሚያከብሩት የኢሬቻ በዓል መከበሪያ ቦታ በአዲስ አበባ መስጠቱን አስተዳደሩ አስታወቀ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኢሬቻ በዓል (ሆረ ፊንፊኔ) ማክበሪያ ቦታ የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ለአባገዳዎች በዛሬው ዕለት አስረክቧል። ከዚህ በተጨማሪ ዛሬ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓሉ የሚከበርበትን ቦታ ከአባገዳዎች ጋር በመሆን በመጎብኘት ዝግጁነቱን አረጋግጠዋል። በኮቪድ-19 ምክንያት የዘንድሮ በዓል በአባገዳዎች በሚወሰን ትንሽ የሰው ቁጥር ብቻ እንደሚከበር ከስምምነት ላይ መደረሱን ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳውቀዋል። የኢሬቻ በዓል ከገዳ ሥርዓት ጋር የተጣመረ ነው፤ ይህም ሃይማኖታዊ ክብረበዓል የገዳን ሥርዓት ሃይማኖታዊ ያደርገዋል፤ ስለዚህ የገዳ ሥርዓት እንደ ትምህርት በመንግሥት ትምህርት ቤቶች መሰጠት አይገባውም … [Read more...] about ኦሮሞዎች በየዓመቱ ለሚያከብሩት ኢሬቻ በዓል ቦታ ተሰጠ
ጠቅላይ ቤተ ክህነት፤ በኦሮሚያ የተፈጸመው ኦርቶዶክሳውያንን የማጽዳት እንቅስቃሴ ነው
የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ጥያቄዎቿን እንዲቀበላት ጠየቀች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሱ ያሉ ተደጋጋሚ ጥቃቶች እንደሚነገረው “በሽግግር ወቅት የሚያጋጥሙ” ተብለው ብቻ የሚታለፉ ሳይሆኑ፣ የተሳሳቱ ርዕዮተ ዓለማዊ ትርክቶችንና ጂኦ ፖለቲካዊ ዳራዎችን መነሻ በማድረግ በተቀነባበረና በተደራጀ ሥልት የሚፈጸሙ ኦርቶዶክሳውያንን የማፅዳት እንቅስቃሴዎች መሆናቸውን ቤተ ክህነት ገለጸች። የኦሮምኛ ቋንቋ ድምፃዊው ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ምክንያት በማድረግ በኦሮሚያ በተለያዩ አካባቢዎች በስድስት ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ 25 ወረዳዎች በሚኖሩ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የገለጸችው ቤተ ክህነት፣ በጥቅምት ወርና በጥር ወር ከጥምቀት በዓል አከባበር ጋር በተያያዘ እንዲሁም በሃጫሉ ሞት ምክንያት በአቢያተ ክርስቲያናትና … [Read more...] about ጠቅላይ ቤተ ክህነት፤ በኦሮሚያ የተፈጸመው ኦርቶዶክሳውያንን የማጽዳት እንቅስቃሴ ነው
የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!?
እንደ መግቢያ ሰሞኑንን ከኮቪድ - 19 ጋር ተያይዞ የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሓኖም አጣብቂኝ ውስጥ መግባቱ ይታወሳል። ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ካወደመው፣ የዘር ፖለቲካን ከሚያራምደው ፍጹም ጽንፈኛና ዘረኛ፣ እንዲሁም በከፍተኛ ደረጃ ኢትዮጵያውያንን በዘራቸው፣ በፖለቲካ እምነታቸው ካኮላሸ፣ ከጨፈጨፈ፣ ቶርቸር ካደረገ፣ በጅምላ ሴቶች እንዲደፈሩና ከነነፍሳቸው ለአውሬ እንዲጣሉ ካደረገ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር/ትህነግ ቴድሮስ የተቀዳ አመራር እንደነበር አይዘነጋም። የተመረጠው በኃያላኑ ዓላማና መልካም ፈቃድ ነበር፤ ኃያላኑ አሁን ፍጥጫ በሚመስል ውዝግብ ውስጥ ይገኛሉ፤ የተመረጠበትን ዓላማ የፈጸመ ከሆነ መወገዱ የማይቀር ይሆናል፤ ካላለቀ ደግሞ ዕድሜ ማራዘሚያ ይሰጠዋል። የቴድሮስ የWHO ምርጫ ወቅቱ የዛሬ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር … [Read more...] about የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!?
ገና (ልደት) እና Hockey
ባለፈው ሳምንት ስለ ልደት በዓል በቤተ ክርስቲያናችን አውደ ምህረት ላይ የቀረበውን በቪዲዮ የተመለከቱ ወገኖች፤ “ኢትዮጵያ በወያኔ እጅ ከመውደቋ በፊት ከጌታችን ልደት በዐል ጋራ ተያይዞ ህዝቡ ገና በሚል ስም የሚጫወተው ጨዋታ ነበረው። ሊቃውንቱ ስለገናው ጭዋታ የሚሉት ነገር ካለ አካፍለን” ብለው ጠይቀዋል። ራሴ እየተጫወትኩት፤ በቅኔውና ባብነቱ ትምህርት እየተማርኩትና እየሰማሁት ያደኩበት ስለሆነ በወያኔ ዘመን ተወልደው ስለ ገናው አመታዊ ጨዋታ ምንም ለማያውቁት ባህላቸውንና ወኔያቸውን ለተዘረፉትና ለጠየቁኝ ኢትዮጵያውያን ከሞላ ጎደል አቅሜ የፈቀደልኝን ለማቅረብ እሞክራለሁ። ከክርስቶስ ልደት ጋራ ተሳስሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገር ከዳር እስከዳር ህዝብ ሲያንቀሳቅ (ሲያቆራቁስ) የነበረ የገናን ጨዋታ የመሰለ ህዝባዊ ነገር ይቅርና፤ ባንዲት መንደር የምትታይ ትንሽ ጥንታዊት … [Read more...] about ገና (ልደት) እና Hockey
የዘመናችን ሲኖድ የቱን ይመስላል?
በዚህ ዘመን ያለው ሲኖድ (ሸንጎ)የቱን ይመስላል? የዮቶርን ሸንጎ? የአርዮስፋጎስን ሸንጎ? ወይስ የክርስቲያኖችን የቱን ይመስላል? ይህንን ጥያቄ የፈጠረብኝ በጥቅምቱ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ በተከሰተው ውዥንብር እንዴት ትመለከቱታላችሁ? በሚል ከህዝብ የቀረበ ጥያቄ ነው። በመጀመሪያ በዚህ ቅዱስ ስብሰባ ላይ ተሳሳቱ የተባሉ ወገኖች የሚታገዱበት የመነጋገሪያ አጀንዳ በሀራ ዘተዋህዶ ድረ ገጽ ተሰራጭቶ ተመለከትን። ቀጠለና አዲስ ተክል አባ ፋኑኤል በገንዘብ በገዙት ጵጵስና ወደ ቤተ ክርስቲያናችን ሰርገው ገብተው በየደረሱበት ህዝብ በማተራመስ ላይ እንዳሉ ከፓትርያርኩ አንደበት ተሰማ። በወቅቱ የቀረበውን ለመረዳት ከፈለጉ በቀይ ቀለም የተጻፈችውን ዓዲስ ተክል የምትለዋን ይጫኑ። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) ቀሲስ አስተርአየ ታህሳስ 7 ቀን 2010 ዓ/ … [Read more...] about የዘመናችን ሲኖድ የቱን ይመስላል?
አባ ፋኑኤል ራሳቸውን ወጉ
መግቢያ አቡነ ፋኑኤል በዜና ቤተ ክርስቲያን ላይ እንዲሰፍር ያደረጉት ሸፍጥ፤ ቢጤያቸውን ለመጋረድና የዘረጉትን የጥፋት መረብ ለማዳን ያደረጉት ሙከራ እንደሆነ ለሁሉም ግልጽ ነው። በዚህ ሸፍጥ ቢጤያቸውን ጋርደው ማዳን ይቅርና፤ ራሳቸውን ከቤተ ክርስቲያናችን አውጥተው መጣላቸውን ለማሳየት የምእመናኑን ውግዘት በቅዱሳት መጻህፍት መዝነው ካወጁት ቀሳውስት፦ ፩ኛ፦ ከሊቀ ማእምራን ዶክተር አማረ ካሣየ ፪ኛ፦ ከቀሲስ አስተርአየ ጽጌ ፫ኛ፦ ከአባ ኃይለ ሚካኤል ወልደ ተክለ ሃይማኖት የተሰጠ መግለጫ እዚህ ላይ ይገኛል። … [Read more...] about አባ ፋኑኤል ራሳቸውን ወጉ
ዘዳግም!
የደመራ ዋና ዓላማ፤ “ሲቃወምና ሲጻረር የነበረውን የዕዳ ጽህፈት ክርስቶስ ከነ ሕግጋቱ በመደምሰስ በመሰቀል ላይ ቸንክሮ ከመንገድ አስወገደው” (ቆላ ፪፡፲፬)። ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው፤ የተደበቀውን እውነት ለመግለጥ፤ በሰው ላይ ተጭኖ የነበረውን ዕዳ ለመደምሰስ፤ ለሰባዊ ክብርና ልዕልና ተጻራሪ የሆነቱን ነገሮች ለማስወገድ ነው። [በሰፊው መረዳት ከፈለጉ ይህን ሰንሰለት ይጫኑ። ደመራ] ሙሴ አራቱን የኦሪት መጻሕፍት ከጻፈ በኋላ፤ በአራቱም መጻሕት የገለጻቸውን ጠቅለል አድርጎ በድጋሚ ያቀረበበት አምስተኛው መጽሐፍ ዘዳግም ይባላል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለሰባዊ ክብርና ልዕልና ተጻራሪ የሆነውን ለማስወገድ የገለጸባቸውን ኃይለ ቃላት ለማስጨበት “አማን አማን እብለክሙ” እያለ በመደጋጋም ተናግሯል። በጸሎተ ቅዳሴያችንም “ተንስኡ ለጸሎት” የሚለውን እንደጋግማለን። ቃጭልም … [Read more...] about ዘዳግም!
የቀሳውስት ድምጽ
በሀገር፣ በሕዝብና በቤተ ክርስቲያን ላይ በደል ሲፈጸም የጥንታዊት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቀሳውስት የሚያሰሙት ድምጽ “ዘወሀብከነ ሥልጣነ በመንፈስ ንኪድ ኩሎ ኃይሎ ለጸላኢ ከመ ንፍታህ ዘኢይትፈታህ” ማለትም፦ “ጠላት ሰይጣን እንዳይፈታ አርጎ የቋጠረውን የችግር ሰንሰለት እንፈታ ዘንድ የቅስናዋን መንፈሳዊት ሥልጣን የሰጠኸን አምላክ” እያልን በምንገልጻት ተልእኮ በጥንታዊት ኢትዮጵያ ኦርቶቶዶክ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ያሰማራንን አምላክ ስሙ የተመሰገነ ይሁን እያልን፤ እኛ ቀሲስ ዶ/ ር አማረ ካሳዬ እና ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ ሐምሌ ፳፰ ቀን ፳፻፮ ዓ/ ምህረት በዋሸንግተን ዲስ በተደረገው ሕዝባዊ ሰልፍ ላይ ይህችን የቤተ ክርስቲያን ድምጽ አቀረብን። ከኛ በፊት በህዝባችንና በአገራችን ላይ መከራና ስቃይ በደረሰባቸው ጊዜዎች ሁሉ፤ አባቶቻችን ቀሳውስት የእምነትና … [Read more...] about የቀሳውስት ድምጽ