የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ድርጅት በ500 ሚሊየን ብር በናዝሬት ከተማ ያስገነባው 7ኛው የኃይሌ ሪዞርት ዛሬ ተመርቋል። በሪዞርቱ የምርቃት ሥነስርዓት ላይ ሻለቃ ኃይሌን ጨምሮ የሪዞርቱ የሥራ ኃላፊዎች መግለጫ ሰጥተዋል። ዛሬ የተመረቀው ሪዞርት ሰፋፊና ምቹ የመመገቢያና የስብሰባ አዳራሾች ጨምሮ 106 የእንግዳ ማረፊያ ክፍሎች፣ የስፖርት ማዘወትሪያ ስፍራዎች፣ የመዋኛ ገንዳዎች እና ሌሎችንም መሠረተ ልማቶችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል። በናዝሬት የተገነባው ሰባተኛው ሪዞርት በ 500 ሚሊየን ወይም በግማሽ ቢሊየን ብር ወጪ ተገነባ መሆኑን ኃይሌ በመግለጫው ገልጿል። ከዚያም ባለፈ 300 ለሚሆኑ ዜጎችም የሥራ ዕድል መፍጠሩን ተናግሯል። ሪዞርቱ በግንባታም ሆነ በአገልግሎቱ ከሌሎች ሪዞርቶች ለየት ባለ መልኩ መቅረቡን የተናገረው ሻለቃ ሀይሌ÷ ከባለ 4 እና 5 ኮኮብ … [Read more...] about የግማሽ ቢሊዮን ብሩ የናዝሬቱ ኃይሌ ሪዞርት ተመረቀ
Socio-Political
ማኅበራዊ-ሽከታ
ከመሬት ጋር በተያያዘ ጉቦኞች እጅ ከፍንጅ እየተያዙ ነው
በጉለሌ ክፍለከተማ ከመሬት ጋር በተያያዘ አገልግሎት ለማግኘት ወደ መስሪያ ቤቱ የሄዱ ተገልጋዮችን ጉዳይ እናስፈጽማለን በሚል ጉቦ ሲቀበሉ የተገኙ ግለሰቦች በትላንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ በወንጀል ድርጊቱ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ከክፍለከተማ እስከ ወረዳ ከተዘረጋው ሠንሠለት በተጨማሪ ደላሎችም ይገኙበታል፡፡ የፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ከተገልጋዮቹ ጋር በመሆን ባደረገው ተከታታይ ክትትል ለአገልግሎት እንዲከፈላቸው የጠየቁትን ገንዘብ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ ኅብረተሰቡም በህጋዊ መንገድ ማግኘት የሚችለውን አገልግሎት ገንዘብ በመቀበል በህገ-ወጥ መንገድ አገልግሎት የሚሰጡ የመንግስት አካላትን በማጋለጥ ግዴታውን እንዲወጣ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪውን አቅርቧል፡፡ የወንጀል ድርጊቱን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃዎች በፌዴራል ፖሊስ … [Read more...] about ከመሬት ጋር በተያያዘ ጉቦኞች እጅ ከፍንጅ እየተያዙ ነው
“ፍትኅ ለአዲስ አበባ” በሚል መሪ ቃል የማኅበራዊ መገናኛዎች ዘመቻ ተጀመረ
ስለ አዲስ አበባ ፍትኅ የሚጠይቅ የማኅበራዊ መገኛ ዘዴዎች ዘመቻ ዛሬ በዋናነት በትዊተር ላይ ተጀመረ። ዘመቻው ዛሬም እንደሚቀጥል አዘጋጆቹ የገለጡ ሲኾን፦ “በአዲስ አበባ የታየውን የመሬትና የኮንዶምንየም ምዝበራ በመቃወም” ፍትኅ ለመጠየቅ የተጀመረ መኾኑንም አክለዋል። በዘመቻዉ ላይ “#ፍትህለአዲስአበባ”፤ “#አዲስአበባ” እንዲሁም “#ኢትዮጵያ” የሚሉ አሰባሳቢ ቃላት (ሐሽታጎች) ጥቅም ላይ ውለዋል። የዘመቻው ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ “ተፈጸመ” ያሉትን አድሏዊ አሠራር እና በደል በመዘርዘር ተቃውሟቸውን እና ቅሬታቸውን ሲያስተጋቡ ተስተውለዋል። የዘመቻው አስተባባሪዎች ባሰራጩት ጽሑፍ፦ “በኢ/ር ታከለ ኡማ አስተዳደር ዘመን በአዲስ አበባ የታለያዩ አድሎአዊ አሠራሮች፤ ጥቅመኝነት፤ የህዝብን ሃብት ማባከን የመሳሰሰሉ ጥፋቶች ተስተውለዋል” ብለዋል። ግድፈቶች … [Read more...] about “ፍትኅ ለአዲስ አበባ” በሚል መሪ ቃል የማኅበራዊ መገናኛዎች ዘመቻ ተጀመረ
ወደ ዛምቢያ ከተሰደዱ 50 ኢትዮጵያውያን አንዱ ግድያ ተፈጸመበት
ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ዛምቢያ ካቴቴ አውራጃ ውስጥ በበሀገሬው ቺቦላያ ነዋሪዎች በተፈጸመ ጥቃት መገደሉን ዛምቢያ ሪፖርትስ ትናንት በድረ-ገጹ ዘግቧል። አምሳዎቹ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ዛምቢያ የገቡት ምዋሚ በተሰኘው ድንበር በኩል ሲኾን፤ ወደ ደቡብ አፍሪቃ ከማቅናታቸው አስቀድሞ ካቴቴ ውስጥ በሕገወጥ ቆይተዋል ሲል የአካባቢው ፖሊስ ተናግሯል። የአካባቢው ነዋሪዎች ኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች ባረፉበት ቦታ በሌሊት በድንገት ባደረሱት ጥቃት ከግድያው ባሻገር ዘጠኝ ኢትዮጵያውያን መጠነኛ የመቊሰል አደጋ እንደደረሰባቸው የአካባቢው ፖሊስ ኮሚሽነር ሉክሰን ሳካላ ገልጠዋል። ከኢትዮጵያውያን ስደተኞቹ መካከል 38ቱ በፖሊስ ሲያዙ ማንነታቸው ያልተገለጡ ኹለት ስደተኞች ግን ማምለጣቸውን የፖሊስ ኃላፊው አክለው ተናግረዋል። የፖሊስ አዛዡ፦ የአካባቢው ነዋሪ በሰፈራቸው ስለመጡ ሰዎች ጥርጣሬ … [Read more...] about ወደ ዛምቢያ ከተሰደዱ 50 ኢትዮጵያውያን አንዱ ግድያ ተፈጸመበት
በአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላን አስመልክቶ የተደረገ ጥናት ውጤት
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በአዲስ አበባ ከተማ የሚፈፀም የመሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላ ጋር በተያያዘ ያደረገውን ጥናት ውጤት ይፋ አድርጓል። የጥናቱ ውጤት ዋነኛ ይዘት ከዚህ በታች ተቀምጧል። በአዲስ አበበ ከተማ መሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላ ጥናት አንኳር፥ • የከተማው አስተዳደር እያየና እየሰማ በሕገ ወጥ እና በተደራጀ መልኩ በወረራ የተያዙ ቦታዎች በፍጥነት ካርታና ፕላን ተሰርቶላቸው ለ3ተኛ ወገን በሽያጭ ተላልፈዋል። በማኅበር እና በግል ለማምረቻና ለንግድ አገልግሎት እንዲውሉ ተደርገዋል፤ በምንም መስፈርት የቤት ተጠቃሚ ሊሆኑ የማይገባቸው ግለሰቦችና ቡድኖች ቤት እና የነዋሪነት መታወቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡ • በዋናነት በመሬት ወረራው ላይ ግንባር ቀደም ተሳታፊ የነበሩት ሰዎች የአርሶ አደር ልጆች … [Read more...] about በአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላን አስመልክቶ የተደረገ ጥናት ውጤት
ኢዜማ፡ በአዲስ አበባ 210ሺህ ካሬሜትር በላይ መሬት ተወርሯል፥ 95ሺህ በላይ ኮንዶ ለማይገባቸው ተሰጥቷል
በአዲስ አበባ በአምስት ክፍለ ከተሞች ብቻ ከ210 ሺህ ካሬ ሜተር በላይ መሬት መወረሩን ኢዜማ አስታወቀ። ፓርቲው አደረኩት ባለው ጥናት በ2012 በጀት ዓመት መስከረም ወር ላይ ለባለዕድለኞች ወጥተዋል ያላቸው ከ95 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ቤቱ ለማይገባቸው ሰዎች መተላለፉንም አስታውቋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ኢዜማ በአዲስ አበባ ህገወጥ የመሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች እደላን በሚመለከት ለአንድ ወር አደረኩት ያለውን የጥናት ግኝት ዛሬ ይፋ አድርጓል። እንደ ፓርቲው ጥናት መሰረት ከሆነ በአዲስ አበባ አምስት ክፍለከተሞች ማለትም የካ፣ ቦሌ፣ ኮልፌ ቀራኒዮ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ እና አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተሞች ከ210 ሺህ በላይ ካሬ ሜትር ቦታዎች በመንግስት አመራሮች ድጋፍ ተወረዋል። ይህ መሬት ገሚሱ በመንግስት ተቋማት ድጋፍ ጭምር ካርታ … [Read more...] about ኢዜማ፡ በአዲስ አበባ 210ሺህ ካሬሜትር በላይ መሬት ተወርሯል፥ 95ሺህ በላይ ኮንዶ ለማይገባቸው ተሰጥቷል
ኃይሌ ጎርጎራ ላይ በአንድ ቢሊዮን ብር ሪዞርት ሊገነባ ነው
ኃይሌ ሆቴሎች በጣና ዳርቻ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ግዙፍና ዘመናዊ ሪዞርት ለማልማት እንዳቀደ ታወቀ። ጎርጎራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በቀጣይ ለማልማት ካሰቧቸው ሦስት የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ ነው። ኃይሌ ኩባንያው በጎርጎራ በዓይነቱ ከዚህ በፊት ከተገነቡ ሪዞርቶች ለየት ያለ ሪዞርትና የመዝናኛ ማዕከል ለመገንባት እንዳቀደ ለሪፖርተር ተናግሯል። ሪዞርቱ የሚገነባው ቀድሞ ጎርጎራ ሆቴል ተብሎ በሚታወቀው በአሥር ሔክታር ቦታ ላይ ነው። ይህ ቦታ የቀድሞ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ማሠልጠኛና የቀድሞ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ያርፉበት የነበረ ሥፍራ ነው። ፕሮጀክቱ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሪዞርትና መዝናኛ ማዕከል፣ ሰው ሠራሽ ባህር ዳርቻና ቪላ ቤቶች ግንባታ ያጠቃልላል። “ጎርጎራ ድብቅ ገነት ነው። ውኃው ንፁህና ጥልቀት ያለው በመሆኑ ለዋናና … [Read more...] about ኃይሌ ጎርጎራ ላይ በአንድ ቢሊዮን ብር ሪዞርት ሊገነባ ነው
መዝገብ የማያውቃቸው 8.4 ሚሊዮን ህጻናት
ባለፉት 5 ዓመታት ከተወለዱ 10 ሚሊዮን ህጻናት ውስጥ 84 በመቶዎቹ ያልተመዘገቡ ናቸው ተባለ። የኢሚግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ባለፉት 5 ዓመታት የመዘገበው የውልደት ኩነት 16 በመቶ ብቻ መሆኑንና ይህም 84 በመቶ የሚሆኑት ተወላጆች በመንግስት ሰንድ ላይ ያልተመዘገቡ እና የማይታወቁ ናቸው ብሏል። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙጀብ ጀማል ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት ከአውሮፓውያኑ 2012 ጀምሮ 10 ሚሊየን ህፃናት ይወለዳሉ የሚል ግምት የነበረ ቢሆንም በወሳኝ ኩነት የተመዘገቡት ግን 2 ሚሊየን ያህሉ ብቻ ናቸው። በዚህ መሀል ያልተመዘገቡትን 8 ሚሊየን ህፃናት ስለመወለዳቸው እና ስለመኖራቸው መንግስት እንደማያውቅ ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት። በህገ መንግስቱ መሠረት ህፃናት እንደተወለዱ በ90 ቀናት ውስጥ መመዝገብ፣ ስም ማግኘት እና … [Read more...] about መዝገብ የማያውቃቸው 8.4 ሚሊዮን ህጻናት
ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራና የነዋሪዎች ቅሬታ!
በአካባቢው ያለውን ህገ-ወጥ የመሬት ወረራ ለሚመለከታቸው አካላት ቢያሳውቁም እስካሁን መፍትሄ አለማግኘታቸውን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሃይሌ ጋርመንት አካባቢ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ህገ ወጦቹ በአካባቢው የሚገኘውን 20 ሜትር ስፋት ያለው መንገድ 10 ሜትር ገፍተው በማጠር አጥብበውታል ሲሉ ነው ለኢዜአ የገለጹት። ጉዳዩን ለወረዳው አስተዳደርና ለክፍለ ከተማው መሬት ይዞታ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ቢያመለክቱም ወንጀሉን ለማስቆም ያላቸው ዝግጁነት አናሳ እንደሆነ ነው የገለጹት። “ቦታውን ካጠሩት ሰዎች ጋር ተደራደሩ” ከሚል ምላሽ በቀር ሌላ ምላሽ እንዳልሰጧቸውም ኢዜአ ዘግቧል። የክፍለ ከተማው መሬት ይዞታ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ “በፅሁፍ ምላሽ ሰጥተናል” ቢሉም የኢዜአ ሪፖርተር ማስረጃ ጠይቆ ማግኘት አልቻለም። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ … [Read more...] about ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራና የነዋሪዎች ቅሬታ!
108 ሕገወጥ ማኅተሞች ተያዙ
የአዲስ አበባ ፖሊስ ጎተራ አካባቢ በሚገኝ አንድ የጋራ መኖሪያ ቤት ውስጥ 108 ህገወጥ ማህተሞች መያዙን አስታወቀ። በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወርዳ 4 ጎተራ ኮንዶሚኒየም ውስጥ 108 ማህተሞች እና የተለያዩ ሀሰተኛ ሰነዶችን ለተለያዩ ህገ-ወጥ ተግባራት ሲጠቀሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሰር መዋሉን ፖሊስ ገልጿል። በከተማችን አዲስ አበባ በተለያዩ ጊዚያት ሐሰተኛ ሰነዶችን በመጠቀም ህገ-ወጥ ተግባር ሲፈፅሙ በፖሊስ ቁጥጥር ውለው በህግ አግባብ የቅጣት ውሳኔ የተላለፈባቸውን ግለሰቦች የወንጀል ድርጊት መረጃ በመስጠት ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክቶችን ማስተላለፋችን ይታወሳል። አሁንም በአንዳንድ አካባቢ መሰል የወንጀል ድርጊቶች ሲፈጸሙ ይስተዋላል በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወርዳ 4 ጎተራ ኮንዶሚኒየም ውስጥ ሀምሌ 1ቀን 2012ዓ.ም. ሁለት ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር … [Read more...] about 108 ሕገወጥ ማኅተሞች ተያዙ