ወያኔና የነፖሊቲካ አጋሮቹ የሚያደርጉትን ለእነሱ የሚመች አከፋፈል ትተን አበሻን ለሁለት እንክፈለው፤ ሆድ ያለውና ሆድ የሌለው፤ ወይም የሚበላና የማይበላ፤ ዛሬ የምናገረው ሆድ ስላለው ወይም ስለሚበላው አበሻ ነው፤ አታውቁት እንደሆነ ተዋወቁት፤ በአጠቃላይ ስንመለከተው ግን የአበሻ ፍቅርም ሆነ ጠብ ለሆድ ነው፤ አበሻን የሚያጣላው፣ የሚያነታርከው፣ የሚያቧጭቀው የሆድ ነገር ነው፤ ለመብላት ነው፤ አንዳንዴም ሎሌውን ለማብላት ነው፤ ግብር ለማግባት ነው። አዳም አበሻ ሳይሆን አይቀርም፤ ሁሉንም ነገር ብላ ከተከለከለው በቀር ብሎ ያስቀመጠው ይመስላል፤በላባችሁ ወዝ ብሉ ተብለው አዳምና ሔዋን መረገማቸውን አበሻ ገና አልሰማም፤ አበሻ የተፈጠረው ገነት ውስጥ ቁጭ ብለህ ያለውን ሁሉ ብላ በተባለበት ጊዜ ነው፤ እግዚአብሔር አበሻን ሁሉንም ብላ ሲለው ምናልባትም በጆሮው ጭራሽ አታስብ ብሎት ይሆናል፤ … [Read more...] about አይ አበሻ! አበሻና ሆድ፤ አንድ
Socio-Political
ማኅበራዊ-ሽከታ
እረፍት የሚነሳው ህምም
እረፍት አደርግ ብየ ከማህበራዊ መገናኛ መድረኩ ገለል ባልኩባቸው እንደ ብርሃን ፍጥነት በሚወረወሩት ባለፉት ጥቂት ቀናት ከበርካታ ወዳጆቸ በርካታ መልዕክቶች ይደርሱኛል። ብዙው መልዕክት ደግሞ የሚያጠነጥነው በጅዳ እና በአካባቢው በተፈናቃይ የኮንትራት ሰራተኞች አሰቃቂ ስቃይ ላይ ያተኮራል ... ለነገሩ የአብዛኞቹ መልዕክቶች ብቻ ሳይሆኑ ከመልዕክቶች ጋር የሚላኩልኝ መረጃዎች እረፍት የሚነሱ ናቸው! ... አዎ ተንቀሳቃሽ ምስል ጭምር በመረጃነት የታጨቀባቸውን የመልዕክት መረጃ ጭብጦች እውነታ ለማረጋገጥ ወደ ጅዳ ቆንስል አመራሁ ... መኪናየን አቁሜ ትንሽ እንደ ተራመድኩ እያለ ከፊት ለፊቴ አንዲት ልጅ እግር ኢትዮጵያዊ ብቻዋን እያወራች ስታልፍ ስመለከት በመደናገጥ ሰላምታ አቅረብኩላት፣ መልስ ሳትሰጠኝ አለፈች! ደነገጥኩና ባለሁበት ቆሜ በአይኔ ተከተልኳት ... በፈጣን እርምጃ … [Read more...] about እረፍት የሚነሳው ህምም
ፈስ አጣርቶ የሚያስቀር ውስጥሱሪ በአሜሪካ እጅግ ተፈላጊ ሆኗል
በእንግሊዝ የተፈበረከው ፈስ የሚያጣራ ውስጥሱሪ በአሜሪካውያን ዘንድ በከፍተኛ ሁኔታ ተፈላጊነቱ እየመጣ መምጣቱ ተሰምቷል፡፡ የአምራች ኩባንያ አፈቀላጤ የሆኑት ሲናገሩ “ከአጠቃላይ ሽያጫችን ውስጥ በአሜሪካውያን የሚገዛው እጅግ ከፍተኛውን ቁጥር የያዘ ነው” ብለዋል፡፡ ታዋቂው የውስጥሱሪ አምራች ሽሬዲስ በቅርቡ ፈስ አጣርቶ በማስቀረት እንዳይሸት የሚያደርግ ውስጥሱሪ ለወንዶችና ለሴቶች ለገበያ ማቅረቡ ከተሰማ በኋላ ሽያጩ በ400% አድጓል፡፡ ኩባንያው እንደሚለው በውስጥሱሪው የውስጠኛ ክፍል ከካርቦን የተሰራ ዞርፍሌክስ የሚባል ጨርቅ የተሰፋ ሲሆን ይህም አማካይ የሽታ መጠን ያላቸውን የፈስ ዓይነቶችን 200 ጊዜ ያህል እንዳይሸቱ የማድረግ ችሎታ እንዳለው አፈቀላጤዋ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ ሲቀጥሉም “ይህ የውስጥሱሪ ለሁሉም የሚያስፈልግ ነው፤ ምክንያቱም ሁሉም ሰው ይፈሳል” በማለት … [Read more...] about ፈስ አጣርቶ የሚያስቀር ውስጥሱሪ በአሜሪካ እጅግ ተፈላጊ ሆኗል
“በአንድ ቀን ትምህርት ፎቶ አንሺ ሆኜ ቁጭ አልኩ” የ69 ዓመቷ አረጋዊ ወ/ሮ ባዩሽ
ካዛንቺስ አካባቢ በልመና የሚተዳደሩ አንድ አይነሥውር ሽማግሌ አሉ፡፡ የሚለምኑት ከካዛንቺስ ስድስት ኪሎና ፒያሳ ለመሄድ ታክሲ ከሚጠብቁ ተሳፋሪዎች ነው፡፡ አንድ ቀን በእለቱ የለመኑትን ገንዘብ ታክሲ እየጠበቅሁ ባለሁበት ቁጠርልኝ አሉኝ፡፡ እስከ ቀኑ 11 ሰዓት አርባ ብር ለምነዋል፡፡ በሌላ ቀን ተመልሼ ጠየቅኋቸው። በልመና ከሚያገኙት ገንዘብ ልጃቸውን ኮሌጅ አስተምረዋል፡፡ ልጃቸው ሥራ ከያዘ ከዓመታት በኋላም ግን ልመና አላቆሙም፡፡ አሁንም እዚያው ካዛንቺስ እየለመኑ ነው፡፡ “ለምን ልመና አያቆሙም?” አልኳቸው፡፡ “ምን ላድርግ ቁጭ ልበል እንዴ?” በማለት እኔኑ መልሰው ጠየቁኝ፡፡ እዚያው ካዛንቺስ የሚለምኑ ሌላ አረጋዊ ከፍተኛ የእይታ ችግር አለባቸው፡፡ በምፅዋት የሚያገኙትን ሳንቲም ይዳብሱና አምስት ሳንቲም ከሆነ መልሰው ይወረውሩታል፡፡ በአንፃሩ የእይታም የአቅምም ችግር … [Read more...] about “በአንድ ቀን ትምህርት ፎቶ አንሺ ሆኜ ቁጭ አልኩ” የ69 ዓመቷ አረጋዊ ወ/ሮ ባዩሽ
“መስቀል የሚያቃጥል (አይደለም)”
በአቃቂ ቃሊቲ ገላን ጉራ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ባለፈው ነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ከሠማይ ወረደ ስለተባለው መስቀል ቅዱስ ሲኖዶስ ውሣኔ እስኪያስተላልፍ ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠባበቅ የአዲስ አበባና የጅማ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ አሣሠቡ፡፡ “መስቀል ከሠማይ ወርዷል አልወረደም? ትክክለኛ ነው አይደለም?” የሚለውን ለመመለስ የግድ ቅዱስ ሲኖዶሡ ጉዳዩን መርምሮ ውሣኔ ሊያስተላልፍበት ይገባል ያሉት ብፁዕነታቸው፤ ይህን ለማድረግም ጉዳዩን ለቅዱስ ሲኖዶሱ ቋሚ አባላት እንዳሣወቁ ተናግረዋል፡፡ መስቀሉ እንደተባለው ከሠማይ የወረደ አለመሆኑ ከተረጋገጠም የቤተክርስቲያኒቱ ሃላፊዎች ይጠየቁበታል ብለዋል-ብፁዕነታቸው፡፡ መስቀሉ ከሠማይ ወረደ በተባለ በ4ኛው ቀን ነሐሴ 27 ቀን 2005 ከሠአት በኋላ ወደ ስፍራው በማቅናት ተገቢውን የፀሎት ስርአት ከካህናቱና … [Read more...] about “መስቀል የሚያቃጥል (አይደለም)”
የደብሪቱ ወተት
ሰፈራችንን መሀል ለመሀል ሰንጥቆ ከሚያልፈው መንገድ በስተቀኝ ሃያ አንድ መኖሪያ ቤቶች ይገኛሉ። ከነዚህ ቤቶች ነዋሪዎች ውስጥ ከአብዛኛዎቹ ጋር የስጋ ዝምድና አለን። በተለይ በአንድ ግቢ ውስጥ የምንኖረው ስምንት ቤተሰቦች ደግሞ የቅርብ - በጣም የቅርብ ዘመዳሞች ነን። በነዚህ ቤቶች ውስጥ አያቶች፣ እናቶች፣ አባቶች፣ አክስቶች፣ አጎቶች፣ አማትና አማቾች ሲኖሩ ከሁሉም የተውጣጣን የልጅ ልጆችም እንገኛለን። ከአጎቶቻችንና ከአክስቶታችን መካከል ሁለቱ ከኛ ዕድሜ ብዙ ስለማይርቁ ቀረቤታችን የጎላ ነው። አሰግድ ገ/እግዚአብሔርና ... አሰግድ ቀልደኛ ነው። በማንኛውም ጊዜ በትንሹም በትልቁም ነገር እራሱን አዝናንቶ ሌላንም ለማስደሰት ይጥራል። የወጣለት ፀሐፊም ነው። እንደዛሬው የትያትር ጥበብ ሳይስፋፋ በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ከሚሉ ጥቂት ተዋናዮች መካከልም አንዱ ነበር። አሰግድ አጎቴ … [Read more...] about የደብሪቱ ወተት
10 American Foods that are Banned in Other Countries
Americans are slowly waking up to the sad fact that much of the food sold in the US is far inferior to the same foods sold in other nations. In fact, many of the foods you eat are BANNED in other countries. Here, I’ll review 10 American foods that are banned elsewhere. (Click here to read) … [Read more...] about 10 American Foods that are Banned in Other Countries
አዲስ ዓመት – በነተበ ሥርዓት
ጊዚያቶች ክንፍ አውጥተው የሚበሩ ይመስላሉ። 2005 አምና ለመሆን በቅቷል። የተፈጥሮን ህግጋት ጠብቆ በዳመና የጠቆረው ዳመና እየገለጠ፣ አበቦች እየፈኩ ምድሪቷ የመስከረም ወር መጥባቱን ብታበስርም፤ በክፉ የወያኔ አገዛዝ ቀንበር ስር ለሚማቅቀው የአገሪትዋ ህዝብ ዛሬም እንጉርጉሮው የሀዘን ነው። የኑሮ ውድነቱ፣ የሰብአዊ መብት ጥስቱ፣ ፍትህ ማጣት እና በመሳሰሉ ስር በሰደዱ ችግሮች እግር ተወርች ተቀፍድዶ ነገን በተስፋ ተሞልቶ አዲስ ዓመት ይጠብቃል ማለት ዘበት ነው። ይልቁንም አዲስ ዓመት ይዞት በሚመጣው የኑሮ ጣጣ የሚቆዝመው ህዝብ ቁጥር እልፍ ነው። ‹‹ትራንስፎርሜሽን›› የሚባል የወያኔ ዕድሜ ማራዘሚያ የተዘጋጀው እቅድ እንደተወራለት በአምስት ዓመት ውስጥ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ህዝብን የሚያሰልፍ አለመሆኑን ሁሉም ተገንዝቦታል። ይልቁንም የህውሃት ግዙፉ ድርጅት … [Read more...] about አዲስ ዓመት – በነተበ ሥርዓት
‹‹ጀርባ የሚልጡ›› ትናንቶች
ለቅሶ ቤት ቁጭ ብለው የሚጨዋወቱ ሰዎች በእጃቸው ካለው የመጫወቻ ካርድ (ካርታ) እኩል ትኩረት ያደረጉበት ርዕሰ ጉዳይ የአዲሱ ዓመት በዓል ገበያ ነበር፡፡ ሽንኩርት በኪሎ 15 ብር መግባቱ የሚገርማቸው ብቻ አልነበሩም፤ ከአገር የጠፋው በሽተኛው ቲማቲም 25 ብር ላይ መተኮሱ ጭምር ለባለካርታዎቹ መነጋገርያቸው ነበር፡፡ ‹‹ለነገሩ አንድ ኪሎ የቲማቲም ዘር ሁለት ሺሕ ብር በገባበት በዚህ ወቅት፣ ገበሬ በስንት ብር ሊሸጥ እንደሚችል መገመት ይቻላል፤›› በማለት የፀረ አረም ኬሚካሎችንና የአትክልት ዘሮችን የምታከፋፍለው ወጣት፣ የዕድምተኛውን ልብ መለስ አደረገች፡፡ ቲማቲም በበሽታ መመታቱ ብቻ ሳይሆን ለዘርም ለዘሪም መጥፋቱ ዋጋውን ሰማይ አድርሶታል ብለን ብንስማማም፣ የበዓሉን እግር ተከትለው የናሩ ምርቶች ግን የሚጋረፉ ናቸው፡፡ ‹‹የሐበሻ›› እንቁላል አንዷ ያውም የቄብ የምታህለው፣ … [Read more...] about ‹‹ጀርባ የሚልጡ›› ትናንቶች
የዛሬዎቹ ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› እና ‹‹ሆያሆዬ››
ኢትዮጵያውያን ልዩ ልዩ በዓሎቻቸውን ስለየበዓላቱ ትርጉም ባላቸው ዝማሬዎችና ጭፈራዎች ያደምቁታል፡፡ ከእነዚህ አንዱ የሆነው የዘመን መለወጫንም ‹‹እንቁጣጣሽ››ን በ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› ያደምቁታል፡፡ እንቁጣጣሽ ሲመጣ ልጃገረዶች ከበሯቸውን ይዘው በየቤቱ እየዞሩ ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› እያሉ ሲጨፍሩ፣ ድምፃዊቷ ዘሪቱ ጌታነህም በየራዲዮ ጣቢያው ‹‹እንቁጣጣሽ እንኳን መጣሽ…›› እያለች በቀጭኑ ድምጿ የምታቀነቅነው ዘፈን ሲሰማ በዓሉን ለመቀበል ያለውን ስሜት ሞቅ ሞቅ ያደርጋል፡፡ ቀደም ሲል ልጃገረዶች ‹‹አበባ አየሽ ሆይን›› ለመጨፈር ተቧድነው እንግጫ ይዘው፣ ከበሯቸውን እየመቱ ከዋዜማ እስከ በዓሉ ዕለት ይጨፍራሉ፡፡ ያኔ የነበረው ጭፈራ የግጥምና የዜማ መፋለስ ችግር አልነበረበትም፡፡ ጨፋሪዎቹም ለዓይን ሞላ ያሉ ነበር፡፡ ጨፍረው ሲያበቁም በዋናነት የሚሸለሙት ቤት ያፈራውን ስለነበር … [Read more...] about የዛሬዎቹ ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› እና ‹‹ሆያሆዬ››










