ፈላጊና ተፈላጊን የሚያገናኙ ደላሎች እስከ 60 ሺህ ብር ኮሚሽን ይከፈላቸዋል ባሎቻቸው ሳያውቁ በውጭ አገር ማህፀን አከራይተው የተመለሱ ሴቶች አሉ ማህፀን ማከራየትም ሆነ መደለል ህገወጥ ነው - የህግ ባለሙያ ማህፀን ለመከራየት ከአሜሪካና ከአውሮፓ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ ባለትዳሮች በመበራከታቸው ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ እንደተስፋፋ ደላሎች የተናገሩ ሲሆን፤ የማህፀን ኪራይና የማህፀን ኪራይ ድለላ ህገ-ወጥ እንደሆነ የህግ ባለሙያ ገለፁ፡፡ የዛሬ 3 ዓመት ወደ ህንድ ሄዳ የማህፀን ኪራይ አገልግሎት እንደሰጠች የተናገረች አንዲት ወጣት፤ የ11 ወር ወጪዋ ተችሎ 250ሺ ብር እንደተከፈላት ገልፃለች፡፡ አሁን ክፍያው በእጥፍ አድጐ 500ሺ ብር መድረሱን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ የማህፀን አከራይዋንና ተከራዮቹን የሚያገናኙ ወኪሎች፤ክፍያው ከሌሎች አገራት ጋር ሲነፃፀር አነስተኛ … [Read more...] about የማህፀን ኪራይ ክፍያ 500ሺ ብር ደርሷል
Socio-Political
ማኅበራዊ-ሽከታ
የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልኝ!
እኔ ወ/ሮ እታገኝ መኮንን ካሣ አድራሻ፡- አዲስ አበባ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 09 የቤት ቁጥር 760/ሀ ነዋሪ ነኝ፡፡ በአሁኑ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 09 ከላይ ቁጥሩ በተገለፀበት ቤት ከ40 ዓመት በላይ ተከ ራይቼ ስኖር በ1990 ዓ.ም በኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ መያዜን አወኩ፡፡ ቤቴንም ሆነ ልጆቼን እን ዲጠብቅልኝና እንዲረዳኝ በማለት ከ1994-1997ዓ.ም ድረስ በውክልና ሰጥቸው የነበረ ሲሆን ከ97 በኋላ ግን ውክልናውን ትቶ የራሱን ቤት ሰርቶ ሄዷል፡፡ ቤቱ እስከታሸገበት ጥር 12 ቀን 2003 ዓ.ም ድረስ ለአቶ ደረጄ ጎዳና ከመንግስት ተከራይ በማስመሰል በቤት ቁጥር 760/ሐ በአቶ ደረጄ ስም የአንድ አመት (በ1998 ዓ.ም) የቤት ኪራይ በስማቸው ቀበሌ ሂዶ ከፍሏል በማለት እኔ ደካማና በሽተኛዋን የፍርድ ቤት ውሳኔ ነው በማለት ቤቴን ጥር 12 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በመ ድኃኒቴ … [Read more...] about የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልኝ!
“ልጄ አካለ ስንኩል ነው እንጂ አእምሮ ስንኩል አይደለም”
አካለ ስንኩል የሆነውን ልጁን በትከሻው በመሸከም በየቀኑ 14.4ኪሜ (9ማይል) በእግሩ በመጓዝ ለሚያመላልሰው አባት መንግሥት በአቅራቢያው ቤት እንደሚሰጠው ተነገረ፡፡ በደቡብ ምዕራብ የቻይና ግዛት የሚኖረው የአርባ አመቱ አባት አካለ ስንኩል የሆነውን የ12ዓመት ልጁን ት/ቤት ለማስገባት ካለው የጸና እምነት የተነሳ ልጁ ራሱን ችሎ መራመድ የማችል በመሆኑ ለመጓጓዣ ባዘጋጀው ለየት ያለ ቅርጫት በመሸከም ከመስከረም ወር ጀምሮ እያመላለሰው መሆኑን የቻይናን ዜና ምንጮችን ጠቅሶ ዴይሊ ሜል ዘግቧል፡፡ ልጁ የሦስት ዓመት ህጻን በነበረበት ወቅት ከወላጅ እናቱ ጋር የተለያየው አባት ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ልጁን ብቻውን ያሳደገው ሲሆን እናቱ ብትለይም ልጁን ብቻውን ለማሳደግ በመወሰን መክፈል የሚገባውን መስዋዕትነት ሁሉ ለመክፈል የዚያኑ ጊዜ መወሰኑን ተናግሯል፡፡ ልጁ እያደገ ሲመጣ ት/ቤት … [Read more...] about “ልጄ አካለ ስንኩል ነው እንጂ አእምሮ ስንኩል አይደለም”
23 ዓመት + አስደንጋጭ + አሳዛኝ = ወዴት እየሄድን ነው?
ተማሪዎች ያለዕድሜያቸው ጫት፣ ሲጋራና ልቅ ወሲብ ይጀምራሉ ሴት የቢሮ ሠራተኛ ሴቶች በወሲብ ንግድ ኑሮአቸውን ይደጉማሉ ኢትዮጵያ ልጆችዋን እየከሰረች ነው ትግራይ ጫት መቃም ክልክል ነው "በስነምግባር የታነፁ ዜጐችን በማፍራት ረገድ አገሪቱ ፈታኝ ሁኔታ ላይ ናት" በአዲስ አበባ ከአንደኛ ደረጃ እስከ ከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች፤ ለከፍተኛ የስነ ምግባር ጉድለቶች እንደተጋለጡ ጥናቶች አመለከቱ፡፡ ሰሞኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ከባለድርሻ አካላት ጋር “ስነምግባር ለእድገት ሁሉ መሠረት ነው” በሚል ርዕስ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ በቀረቡት ጥናቶች በተለይ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፤ በየትምህርት ቤቶቹ አካባቢ ባሉ ህገወጥ የአልኮል፣ የአደንዛዥ እጽ መጠቀሚያ እና የወሲብ ፊልሞች ማሣያ ቤቶች መበራከት የተነሣ ለችግሩ ተጋላጭነታቸው … [Read more...] about 23 ዓመት + አስደንጋጭ + አሳዛኝ = ወዴት እየሄድን ነው?
ወገንን በመርዳት ለኢትዮጵያ ያለን ፍቅር ይገለጻል!
የዶክተር ካትሪን ሃምሊን እና የባለቤታቸው በዶ/ር ሬጅ ሃምሊን ግማሽ ክፍለ ዘመን የተጠጋው በጎ ምግባር የሚያሳዩ ድርሳናትን ስፈታትሽ አድሬ አረፋፈድኩበት ። "የፊስቱላ ተጠቂዎች የተስፋ ታሪክ " በሚል በአንድ ወቅት በፊሱትላ በሽታና በዶክተር ካትሪን እና በቤተሰባቸው በስራ ባልደረቦቻቸው ተጋድሎ ዙሪያ የቀረበ በእጀ ነበረ ከሲድኒ አውስትራልያ መስፍን ማሞ ተሰማ ያቀረበልንን ድንቅ በበቂ መረጃ ደጋግሜ አነበብኩት። "ዶ/ር ካትሪን ሀምለን በአሁን ሰአት በአውስትርሊያ ግዛት በአንድ የባህር ዳርቻ በሚገኘው ምቾታማና የናጠጠ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ቀሪውን የህይወት ዘመናቸውን እንኳ ለማሳለፍ አልፈለጉም። ዛሬም በዚህ እድሜያቸው ከሃገር ሃገር እየዞሩና እየተንከራተቱ ዕርዳታ በመጠየቅ የፊስቱላን በሽታ ከምድረ ኢትዮጵያ ለማስወገድ እንዲቻል የፋይናንስ፤ የማቴሪያልና የባለሙያ ኃይልን እያደራጁ … [Read more...] about ወገንን በመርዳት ለኢትዮጵያ ያለን ፍቅር ይገለጻል!
ሶስት ነገር ያጣችው ሳልዋ – አሜሪካ
አሜሪካ የመጣችው ከ27 አመት በፊት ነበር። ሁለት ልጆች የወለደችለት ባለቤትዋ በሞት ሲለያት ታዳጊ ህጻናት ልጆቿን ይዛ በሱዳን በኩል አድርጋ አሜሪካ መጣች። ሳልዋ ትባላለች፤ የጠይም ቆንጆ ናት። በአሜሪካ ዲሲ ከተማ ብዙዎች የሚያውቋት በታታሪ ሰራተኛነቷ፣ በሳቅ ጨዋታዋ፣ እንዲሁም በመልካም ባህርይዋ ነው። ጥሩ ስራና ገቢ የነበራት ሳልዋ በፍቅር ከቀረበችው ሃበሻ ጋር በአብሮነት መኖር ይጀምራሉ። ለረጅም አመት ብዙዎችን የሚያስቀና ፍቅር እንደነበራቸው የሚያውቋቸው ይናገራሉ። በድንገት የሳልዋን ልብ የሚሰብር ሁኔታ ይፈጠራል፤ የምትወደውና ልጅ ያልወለደችለት ፍቅረኛዋ በድንገት በሞት ይለያታል። ሃዘኑን መቋቋም የተሳናት ሳልዋ ይባስ ብሎ ሁለቱ ልጆቿ ጥለዋት ወደ ሌላ ከተማ ሄዱ። ለ17አመታት ገደማ ጠይቀዋት አያውቁም፤ እሷም ልጆቿ የት እንዳሉ አታውቅም። ሶስት ነገር ያጣችው ሳልዋ ጤናዋ … [Read more...] about ሶስት ነገር ያጣችው ሳልዋ – አሜሪካ
“በሴቶች ላይ የሚደረግ አካላዊ ጥቃትና ትንኮሳ ይቅር!”
ነገ ከተራ፣ ከነገ በስቲያ ጥምቀት ስለሚከበር ቢሮ ውስጥ ያለን ኢትዮጵያውያን ጥምቀትን አይተው ለማያውቁ ፈረንጅ ባልደረቦቻችን ስለ በአሉ ዘርዘር አድርገን እያወራን ነበር፡፡ ወሬው ሲሟሟቅ አንዱ ልጅ "the best part is throwing lemon (lime) on the girls!" አለ፡፡ ‹‹ከሁሉ ከሁሉ ደስ የሚለኝ ግን ልጃገረዶች ላይ ሎሚ መወርወር ነው›› እንደማለት ፡፡ ፈረንጆቹ ግራ ተጋቡ፡፡ ‹‹በበአል ምድር ምን ይሁን ብላችሁ ነው ሴቶች ላይ ሎሚ የምትወረውሩት?›› ብሎ ጠየቀ አንዱ፡፡ ‹‹ለፍቅር ለመጠየቅ ነዋ!...ሎሚ የተወረወረባት ሴት ደስ ይላታል፡፡ እንደውም ልጃገረዶች ወደ ጥምቀት ሲሄዱ አዲስ ልብስ ወይ ያላቸውን አጥበውና ተኩሰው ለብሰው፣ ተኳኩለው ነው የሚሄዱት፡፡ ያውም፤ ‹‹ እንደው ቀንቶኝ ሎሚ የሚወረውርብኝ አገኝ ይሆን!›› ብለው አልኩት፡፡ ይባስ ግራ … [Read more...] about “በሴቶች ላይ የሚደረግ አካላዊ ጥቃትና ትንኮሳ ይቅር!”
ኢትዮጵያን ለማየት ፣ ጥምቀት በጎንደር ማክበር…!
የከተራው በአል ከተራ ምንድን ነው? ከሚለው ትርጓሜ እንነሳ ... በየዓመቱ የጥምቀት በዓል በድመቀት ይከበራል፡፡ ከበዓሉ በፊት የከተራ በዓል የሚከበርበትን ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ገለጻ ከተራ ከበበ ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡ የጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላል፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥል ይውላል፡፡ የምንጮች ውኃ ደካማ በመሆኑ እንዲጠራቀም ይከተራል ፣ ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ ይገደባል፡፡ ከተራ በዓል በየዓመቱ በበዓለ ጥምቀት ዋዜማ ጥር 10 ቀን ይውላል ። የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታይ ምእመናን ሲወርድ ሲዋረድ ይዘው በመጡት ሃይማኔታዊና ባህላዊ እሴት መሰረት በጥምቀትን በዓል ዋዜማ … [Read more...] about ኢትዮጵያን ለማየት ፣ ጥምቀት በጎንደር ማክበር…!
አሳዛኙ የትውልድ ህይወት በሳውዲ አረቢያ «ጂዛን» ከተማ!
ጂዛን እየተባለ በሚጠራ የሳውዲ አረቢያ ግዛት ውስጥ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌለውን ጨምሮ ከ50 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን እንደሚኖሩ ይነገራል። የጂዛን ከተማ ሳውዲ አረቢያን ከየመን የሚያዋስን ከተማ እንደመሆኗ በባህር የሚመጡ ብዛት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ወደ ሪያድ እና ጅዳ ከተማ ለማቅናት በመሸጋገሪያነት እንደሚጠቀሙባት ይነገራል። በዚች የድንበር ከተማ አያሌ ኢትዮጵያውያን ጉዳዩ በወል በማይታወቅ ምክንያት ያለ ፍርድ ለ 4 እና 5 አመታት ታስረው የሚሰቃዩባት ከተማ መሆኗን የሚነገሩ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ወደ ሃገር ለመመለስ ጥያቄ ያቀርቡ አያሌ ወገኖቻችንም በሪያድ የኢትዮጵያን ኤንባሲ እና ለጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ያቀረቧቸው ጥያቄዎች እስካሁንም ምላሽ ባለማግኘቱ ህይወታቸው አደጋ ውስጥ መሆኑን ይናገራሉ ። ይህ በዚህ እንዳለ ከሁሉም በላይ እስከፊ አስከፊ በለው የሚገልጹት ምንጮች … [Read more...] about አሳዛኙ የትውልድ ህይወት በሳውዲ አረቢያ «ጂዛን» ከተማ!
ፖለቲካና ሃይማኖተኝነት የሚያቃርናቸው ነገር አለን?
ፖለቲካ የሚለው ቃል የባዕድ ቃል ነው እምነተ-አሥተዳደር ማለት ነው፡፡ ከባዕድ ከመምጣቱም ቃሉንና ተግባሩን በመልካም ጎኑ ቀምሰን ሳናጣጥመው ወዲያውኑ ምሬቱን ስላሳየን ለቃሉና ለተግባሩ መልካም ስሜት የለንም፡፡ አንድ አባባልም ፈጥረንለት ከሥነ-ቃሎቻችን ቀላቅለንለታል ‹‹ፖለቲካንና ኮረንቲን በሩቁ ነው›› የሚል፡፡ በእርግጥ ግን ፖለቲካን ርቆ መራቅ ይቻላል? ለዚህ ቃልና ለተግባሩ ባለን ጥሩ ያልሆነ አመለካከት የተነሣ ፖለቲካ ያለውን የሀገርንና የሕዝብን እጣ ፈንታ የመወሰንን ያህል ግዙፍ አቅምና ሚና ዘንግተን ፖለቲካንና ፖለቲከኛነትን ጭንቅላታችን ውስጥ የጭራቅ ምስል ሥለን በመፍራት በመጥላትና በመሸሽ በዜግነታችን ለሀገራችን ልናበረክተው የሚገባንን ተግባርና አገልግሎት እንዳናበረክትና ሀገሪቱም በፖለቲካ ምክንያት ከሚከሰቱ ትብትብ ችግሮች እንዳትወጣ አድርጓታል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ … [Read more...] about ፖለቲካና ሃይማኖተኝነት የሚያቃርናቸው ነገር አለን?