ሥልጣን የያዙ ሰሞን ሞት የቀደማቸው መለስ ሲጠየቁ የኢትዮጵያን ሕዝብ በቀን ሦስት ጊዜ እመግባለሁ ወይም ሲመገብ አያለሁ የሚል የውሸት ተስፋ ሰጥተው ነበር፡፡ “የቀማኛ ኢኮኖሚ አቀንቃኝ” የነበሩት መለስ ለሥልጣናቸው ማራዘሚያ ጥቂቶችን በሃብት እንዲወጠሩ ሲያደርጉ የተቀረውን ኢትዮጵያዊ በቀን ሶስቴ ቀርቶ በሶስት ቀን አንዴ የማይመገብ አድርገውት ተሰናብተዋል፡፡ “ሌጋሲያቸውን እንጠብቃለን፤ እናስጠብቃለን” የሚሉት ያሁኖቹ ዘራፊዎችና ተላላኪዎች አገር በሁለት አኃዝ አድጋለች፤ ኢኮኖሚው ዓለምን እያስደነቀ ነው፤ ህዳሴ ነው፤ ውዳሴ ነው፤ … በማለት በቁማቸው ይዋሻሉ፤ የጥቅም ተካፋዮቻቸውም ይህንኑ ይዘው በየቀኑ ሲያናፉ ይውላሉ፡፡ ህወሃት ስለዘረጋው የዘራፊ፤ የቀማኛ፤ የሌባ፤ ኢኮኖሚ ብዙ ሊባልበት ይቻላል፡፡ ሌብነቱን ደግሞ መለስ ራሳቸው መስክረው ነው የሞቱት፡፡ “ያስቸገረን የመንግሥት … [Read more...] about የመለስ “ሌጋሲ” – የድርብ አኻዝ ዕድገት ውጤት
Socio-Political
ማኅበራዊ-ሽከታ
የኛ የነዳጅ ዋጋ የሚቀንሰው መቼ ነው?
ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ የመጣው የዓለም የነዳጅ ዋጋ አሁን ደግሞ ሊብስበት ነው፡፡ በኢራን ላይ የተጣለው የኢኮኖሚ ማዕቀብ ትናንት በመነሳቱ በዓለም ገበያ ለአንድ በርሜል ድፍድፍ ዘይት የሚከፈለው ዋጋ ከ31 ዶላር ወደ 28 ዶላር ገብቷል፡፡ ይህ በአንድ ቀን የታየ የዋጋ ልዩነት ለወደፊቱ እየባሰ ሊሄድ እንደሚችል የዓለም የኢኮኖሚ ጠበብት በመናገር ላይ ይገኛሉ፡፡ በኢኮኖሚክስ Principle መሰረት ዋጋ ሲቀንስ የፍላጎት መጠን ይጨምራል፡፡ የገንዘብ የመግዛት አቅምም ይጨምራል፡፡ ዋጋውን ተከትሎ በአቅርቦት ላይ የሚደረግ ቅናሽ ካልታየ በዚያው ዋጋ ብዙ ምርትና አገልግሎት መግዛት ይቻላል፡፡ አቅራቢው ምርቱን የሚጨምር ከሆነ ደግሞ (በኢራን ላይ የተጣለው ማዕቀብ በመነሳቱ የነዳጅ አቅርቦቱ መጨመሩን ልብ ይሏል) ገዥው የሚገዛው ምርትና አገልግሎት እየጨመረ ይሄዳል፡፡ ስለዚህ እጥረት … [Read more...] about የኛ የነዳጅ ዋጋ የሚቀንሰው መቼ ነው?
ጥምቀትና ጎንደር Vs የትዝብት ወግ
“ጥምቀትን በጎንደር መታደም መባረክ ነው” ይህ የብዙሃኑ የእምነቱ ተከታዮች የምስክርነት ቃል ነው፡፡ ጥምቀትና ጎንደር የገጠሙ እለት እንኳንስ ለጎብኝዎች ለነዋሪዎችም ታይተው አይጠገቡም፡፡ የጎንደር ጥምቀት በዓል ከመላ ኢትዮጵያ አከባበር የሚለይባቸው በሁለት ተያያዥ ምክንያቶች ይመስለኛል፡፡ ከቀድመው የመሳፍንት እና የአፄዉ ስርዓት ጋር በተያያዘ ከተማዋ ለረዥም ዓመታት መናገሻ ከተማ ሆና መቆየቷ፣ በጊዜው የነበረው ኃይማኖታዊ መንግስት በመሆኑ አብዛኛው ነዋሪ ጥብቅ የኦርቶዶክስ ክርስትና ኃይማኖት ተከታይ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ከሌላው አካባቢ (ከተማ) በተለየ መልኩ “የአርባ አራቱ ታቦታት” መገኛ መሆኗ የመጀመሪያው ምክንያት ሲሆን፤ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በአስራ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ከአፄ ፋሲል ቤተመንግሥት ምስረታ በኋላ ከቤተ መንግሥቱ በስተ ምዕራብ በኩል አራት … [Read more...] about ጥምቀትና ጎንደር Vs የትዝብት ወግ
ለድርቁ አስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል ይቋቋም!
* ከአገዛዝ ለውጥ በፊት ችጋር ይቀድማል? * “በአሁኑ ጊዜ ችጋሩ እንደ 1977 ሆኗል!” በኢትዮጵያ ላለፉት ፴ ዓመታት ያለታየ ችጋር ተከስቷል። ድርቁና ረሃቡ ከዚህም በላይ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ኢህአዴግን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት ይፋ እያደረጉ ነው። “የምግብ ዋስትናን አረጋግጫለሁ” በማለት ሲወተውት የኖረው ህወሃት ተገዶ ያመነው ችጋር ከ፩፱፯፯ ድርቅ በላይ የከፋ እንደሚሆን ስጋት አይሏል። ከዚህ በፊት እንደተከሰቱት ለውጦች ይህኛውም የአገዛዝ ለውጥ ሊያስከትል እንደሚችል ተነገረ። በአስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል መቋቋም እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ ህወሃት ከድርቅ እና ድርቅን ተከትሎ ከሚገኝ ዕርዳታ ጋር በተያያዘ ካለው አስጸያፊ ተሞክሮ በመነሳት ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንደሚሉት ከድርቁ ጋር በተያያዘ ፍትሐዊነት ያሳስባቸዋል፡፡ ሲያብራሩም በከፍተኛ የሙስና እና የአድልዖ … [Read more...] about ለድርቁ አስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል ይቋቋም!
ሥደት
ቦሳሶ፣ ሶማሊያ ቦሳሶ በገልፍ ባህረ ሰላጤ ደቡባዊ ክፍል፣ሶማሊያ ጠርዝ ላይ የምትገኘው ከተማ፣ ካርታ ላይ ሲመለከትዋት፣ ያፍሪካ ቀንድ ላይ የተቀመጠች ዝምብ ትመስላለች። አፈ ታሪክ ስለከተማዋ አሰያየም እንዲህ ይላል። ቦሳሶ የቀድሞ ሥያሜዋን ያገኘችው ካንድ ታዋቂ ነጋዴ ሥም ነበር - ባንዳር ቃሲም ከተባለ ነጋዴ። ቃሲም ከተማ እየተባለች ትታውቅም ነበር። ነጋዴው፣ ባንዳር ቃሲም ደግሞ እጅግ በጣም የሚያፈቅራት ቡሳስ የተባለች ግመል ነበረችው። ሥለዚህ ከተማዋ ከጊዜ በኋላ በቃሲም ተወዳጅ ግመል ቡሳስ ተብላ ተሰየመች። እያደር ከቡሳስነት ወደ ቦሳሶ ተቀየረች። አለምሰገድና ባለቤቱ ምህረት፣ ምህረትያንድ አመት ልጃቸውን አቅፋ፣ ከቦሳሶ ተነስተው ከሦስት ሰዓት ጉዞ በኋላ ማሬሮ ገብትዋል። ማሬሮ ገደላማ ናት። ካርቶን አንጥፈው የሚቆረቁረው መሬት ላይ ተቀመጡ። አለምሰገድ ለራሱና ለምህረት … [Read more...] about ሥደት
የእኔ፣ ያንተ፣ የእናንተ፣ የእኛ ተጠቂዎች!
የብላቴናው መሀመድን እናት እርዳታ አድራጊ ወገኖቸ የቻልኩትን እርዳታ ለመሰብሰብ ወጣ ባልኩበት አጋጣሚ ስልክ ተደወለልኝ። አነሳሁት፣ ከሰላምታ በኋላ "ጠፋህ? የት ነው ያለህ?" ከሚለው አጭር የተለመደ የሰላምታ ማጀቢያ በኋላ ወዳጀ ወደ መልዕክታቸው ገቡ ... "አንተ ነብዩ የት ጠፋህ?" ሲሉ ደገሙና ስመለጥፋቴ ጠይቀውኝ ሲቀጥሉ "ናና አንድ እህት ከጅዳ ቆንስል በር ወድቃለች፣ ጸሀይ እየደበደበ አድክሟታል! እነሱ (የቆንስል ሰዎች ማለታቸው ነው) ቢነግሯቸው አይሰሙም። ሌላም ሶስት እህቶች ከቆንስሉ አጠገብ ካለው ንጉድ ፉአድ ሆስፒታል ያለ ጠያቂ ተኝተዋል። ጎብኟቸውና ችግራቸውን ተረዱ ወይ መፍትሄ ፈልጉ ወይ ወደ ሀገር ስደዷቸው ብል የሚሰማ የለም! አንተን ከሰሙህ ናና እያቸው!" ብለው ቁጣ የተቀላቀለበት መልዕክት አስተላለፈውልኝ ተጣድፈው ስልኩን ዘጉት ... ! የእኒህ ወንድም … [Read more...] about የእኔ፣ ያንተ፣ የእናንተ፣ የእኛ ተጠቂዎች!
የኮንትሮባንድ ንግድ እንደ ተቋም
በሻሸመኔ አካባቢ የኮንትሮባንድ ንግድ ተቋማዊ ቅርጽ መያዙን የሚያሳይ መረጃ ጠቆመ፡፡ ሌሎች በኮንትሮባንድ ንግድ እንዳይሳተፉ የሚከለክለው ሕግ የሚጸናባቸው ከህወሃት ራቅ ያሉ የኅብረተሰብ ክፍሎች መሆናቸው ድርጊቱን “ማስመጥ” አሰኝቶታል፡፡ ዜጎችም “የኮንትሮባንድ ንግድ ትርጉሙ ምን ይሆን?” እያሉ ነው፡፡ የኮንትሮባንድ ንግድ በህጋዊነት በተለይ የሚፈጸመው ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም ላለፉት 25 ዓመታት በግፍ እየገዛ ባለው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ህወሃትና በአፍቃሪዎቹ መሆኑን በማረጋገጥ የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) በዓይን ምስክርነት የታዘቡትን በፎቶ የተደገፈ መረጃ ልከውልናል፡፡ ዜናውን እማኝ ዘጋቢው ይላኩት እንጂ በድፍን አገሪቱ ህወሃቶች፣ የህወሃት አገልጋዮች፣ የህወሃት ሽፋን ሰጪዎች፣ ነባር ተጋዳላዮች፣ ተላላኪዎች፣ ወዘተ በዚህ ሥራ እንዲሰማሩ … [Read more...] about የኮንትሮባንድ ንግድ እንደ ተቋም
ሠራተኛውን ማን አቃጠለው?
የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) ከጥቂት ቀናት በፊት በአፋር ክልል ሃዳር ወረዳ ኤሊ ውሃ ከተማ ቅዳሜ መስከረም 22፤2008 ዓም ስለተፈጸመው ግድያ መረጃ ልከውልናል፡፡ ከመረጃ አቀባያችን ጋር በተደጋጋሚ በተላላክነውና ባቀረብነው በርካታ ጥያቄዎች መሠረት ያገኘነው መረጃ ይህንን ይመስላል፡- እጅግ ዘግናኝ የሚባለው ግድያ የተፈጸመው ከላይ በተጠቀሰው ሥፍራ በሚገኘው የቻይና መንገድ ሥራ ፕሮጀክት እየተባለ በሚጠራው ግቢ ውስጥ ነው፡፡ የእማኝ ዘጋቢው በራሳቸው አገላለጽ እንዲህ ዘግበውታል፡- (የላኩልን የእንግሊዝኛ ፊደላትን በመጠቀም ሲሆን ወዳማርኛው እንዲህ መልሰነዋል) “ወንጀሉ የተፈጸመው ቅዳሜ መስከረም 22፤2008 ዓም በአፋር ክልል ሃዳር ወረዳ በኤሊውሃ ከተማ ግቢ ተብሎ በሚጠራው የቻይና መንገድ ሥራ ፕሮጀክት ውስጥ ነው፡፡ የተቃጠለው ልጅ ወልዱ ይባላል፡፡ በ(ፕሮጀክቱ) … [Read more...] about ሠራተኛውን ማን አቃጠለው?
“ሙቅ በገንፎ ሲደገፍ”
በአገሪቱ የኤሌክትሪክ ኃይል መሥሪያ ቤት ላይ ኅብረተሰቡ የሚያሰማው እሮሮ ኤሌክትሪኩ መጥፋቱ ብቻ አይደለም፡፡ መብራቱ ሄዶ ሲመጣ የሚያደርሰው ጥፋት የትየለሌ ነው፡፡ የኤሌክትሪኩ ኃይል መጠን ከመደበኛው ውጭ ከፍና ዝቅ ሲል የሚያደርሰው ጥፋት ቤት ይቁጠረው፡፡ ማቀዝቀዣው፣ ቴሌቪዥኑ፣ አምፖሉ፣ ልዩ ልዩ "ቻርጀሮች" የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስ ውጤቶች ተቃጠሉብን የሚል የሕዝብ እሮሮ በየጊዜው ይሰማል፡፡ የሚመለከተው መሥሪያ ቤት ፈጣን ምላሽ ከመስጠት ይልቅ አገልግሎት የማይሰጠውን "905" ላይ ደውላችሁ አስመዝግቡ ከማለት ያለፈ መልስ የለውም፡፡ "የኤሌክትሪክ ምሰሶው ሊወድቅብን ነው፣ ዘሟል፣ ኧረ ድረሱልን" እያሉ ለሚወተውቱም ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዳልተቻለም ማስረጃ ከሚሆኑ ትዕይንቶች (በፎቶዎቹ የሚታዩት) መካከል በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 እንደራሴ አካባቢ ያሉ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች … [Read more...] about “ሙቅ በገንፎ ሲደገፍ”
ሰቆቃ በማዕከላዊ
‹‹እጄን ወደ ላይ አስረው ብልቴ ላይ ሀይላንድ አንጠልጥለውበታል፡፡ ሴቶቹ ሀይላንዱን የሚበቃቸውን ያህል ያወዛውዙታል፡፡ በዚህም ምክንያት ከጥቅም ውጭ ሆኗል፡፡ የዘር ፍሬየን ከጥቅም ውጭ አድርገው ዘሬን እንዳልተካ አድርገውኛል፡፡ ሽንቴንም መቆጣጠር አልችልም፡፡›› አበበ ካሴ እኔ አበበ ካሴ እባላለሁ፡፡ የሰሜን ጎንደር ተወላጅ ነኝ፡፡ በማዕከላዊ እስር ቤት ከ5 ወር በላይ ታስሬለሁ፡፡ ከዚህ መካከል 4 ወር ከ25 ቀናት በጨለማ ቤት ተቆልፎብኝ ቆይቻለሁ፡፡ ማዕከላዊ በነበርኩበት ወቅት የሁሉም እግርና እጆቼ ጥፍሮች ተነቅለዋል፡፡ አንዳንድ ቀን እጄ ላይ የሆነ ነገር ስለሚወጉኝ ጥፍሮቼ ሲነቀሉ አላውቅም፡፡ ስነቃ ነው መነቀላቸውን የማውቀው፡፡ ከዛም ቁስሉን እየነካኩ ያሰቃዩኛል፡፡ ማደንዛዣ ለምን እንደሚወጉኝ አላውቅም፡፡ ጥፍሮቼን ሲነቅሉኝ ብቻ ሳይሆን ሌላ ጊዜም ራሴን እንድስት … [Read more...] about ሰቆቃ በማዕከላዊ