• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አነጋጋሪው የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የፖሊሲ ስልጠና

August 28, 2014 06:11 am by Editor 1 Comment

ተማሪዎችና የፖለቲካ ተቋዋሚ ፓርቲዎች በኢትዮጵያ ፖሊሲ ላይ ያተኮረው ለከፍተኛ ትምሕርት ተቋማት ተማሪዎች የሚሰጠውሥልጠና ከጥሪው አንስቶ በግዳጅ የሚካሄድ መሆኑን ነው የሚናገሩት የኢትዮጵያ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የሁለት ሳምንታት የፖሊሲ ስልጠና ላይ መሆናቸውን መንግስት አስታውቋል ።

ነሐሴ የተጀመረው ይኽው ስልጠና ተማሪዎች በግዳጅ የሚሳተፉበት መሆኑን አንዳንድ ተማሪዎችና ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ይናገራሉ። መንግሥት ግን ይህን ያስተባብላል።

ተማሪዎችና የፖለቲካ ተቋዋሚ ፓርቲዎች በኢትዮጵያ ፖሊሲ ላይ ያተኮረው ለከፍተኛ ትምሕርት ተቋማት ተማሪዎች የሚሰጠውሥልጠና ከጥሪው አንስቶ በግዳጅ የሚካሄድ መሆኑን ነው የሚናገሩት። በተለይ በስልጠናው የማይሳተፉ ተማሪዎች በመጪው አመት የትምህርት እድል እንደማያገኙ ይገልፃሉ ።ከዚህ በተጨማሪ የትምህርት ነጻነትና ፖለቲካዊ ሰበካ በመርህ ደረጃ አብረው የማይሄዱ ሆኖ እያለ ተማሪዎችም ይህን አስመልክቶ ቅሬታቸውን እንዳያሰሙ ተቃውሞ እንደገጠማቸው ነው የሚገልፁት። በትምህርት ላይ ሳሉ የኢህአዴግ አባል የሆኑ ተማሪዎች በኩል መመዝገባቸውንና የስልጠና ቅጽ መሙላታቸውን በስልጠናው የሚሳተፉ ተማሪዎች ይናገራሉ። ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ አንድ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ የስልጠናውን አጀንዳዎች ያብራራል።

ካሁን ቀደም ምላሽ ያላገኘው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጥያቄ በቅድሚያ ምላሽ ሊሰጥበት ይገባል የሚል ተቃውሞ መነሳቱን ይኽው የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ተናግሯል። ተማሪው ስልጠና የሚሰጥባቸው አካባቢዎች በፌዴራል ፖሊስ መከበባቸውንና ተማሪዎች ከቅጥር ግቢው መውጣት መከልከላቸውንም ገልጿል። ተማሪው እንዳለው በስልጠናው የሚሳተፉ ተማሪዎች የተሰጣቸውን የስልጠና ሰነድ በማቃጠል ተቃውሟቸውን አሰምተዋል።

ካልተመዘገቡና ካልተሳተፉ በመጪው አመት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የጀመሩትን ትምህርት ለመቀጠል እንደማይችሉም ጨምረው ተናግረዋል።semayawi

ተቃዋሚው የፖለቲካ ፓርቲ ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው ሳምንት ይህን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ በስልጠና አመካኝቶ የራሱን አስተሳሰብና ርዕዮተ ዓለም በተማሪዎች ላይ እየጫነ መሆኑን አስታውቋል። የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ስለሺ ፈይሳ ስልጠናውን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት የትምህርት ተቋማት ከፖለቲካ ጫና ነፃ መሆን እንዳለባቸው ይናገራሉ። እሳቸው እንደሚሉት ከሆነ አገሪቱ ካለችበት አስቸጋሪ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ አኳያ ይህን አይነት ስልጠና ትልቅ ወጪ የሚጠይቅ ስለሆነ ከየትኛው በጀት ተወስዶ እየተካሄደ መሆኑ ግልጽ ስላልሆነ ሃብት ማባከን ነው ።

መንግስት በበኩል ሥልጠናው በግዳጅ የሚስጥ እንዳልሆነና የትምህርት ነጻነትን እንደማይጋፋ ነው ያስታወቀው። በአምቦ፤ ወለጋ፤መዳወላቡና ደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ተቃውሞዎች አሉ ቢባልም አቶ ሬድዋን ሁሴን ግን የፖሊሲ ስልጠናው ያለምንም እንከን እየተካሄደ መሆኑን ይናገራሉ።

በአሁኑ ወቅት በሃገሪቱ ባሉ ከ30 በላይ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ ከስምንት መቶ ሺ በላይ ተማሪዎች በስልጠናው እንደሚሳተፉ ተገልጿል። (ፎቶ ከፋይል ማህደር)

(ምንጭ: የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ DW: መርጋ ዮናስ እና ነጋሽ መሐመድ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. bini negn says

    September 12, 2014 12:59 am at 12:59 am

    temariw tmhrtun cherso wede sera sigeba yemiyasfetsmew yezihn ager polici new tadiya gnzabe endinorachew madregu mnu lay new metfonetu,,uof were telan

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule