• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አባዱላ ወደ ጨፌ ወይስ ወደ ሸቤ?

October 10, 2017 12:36 am by Editor 1 Comment

የሰበር ዜና ልክፍት የተጠናወተው የዘመኑ “ሚዲያ” የአባዱላን ከአፈጉባኤነት መልቀቅ በሰበር ዜናነት ማናፈሱ ቆም ብሎ ላየው ራስን ትዝብት ላይ የሚጥል ነው። የአባዱላ መልቀቂያ ማስገባት “ምስጢር” በቅርቡ የሚለይለት ቢሆንም በህወሓት ተለክቶና ተጠፍጥፎ የተሠራ ድርጅትና ስብዕና ያለው ለዚህ ዓይነት የሞራል ልዕልና ይደርሳል ብሎ መገመት ህወሓትን ካለማወቅ ወይም ራስን ከመሳት የሚመነጭ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም።

በበርካታ የሙስና ተግባራትና ህይወት ማጥፋት አለበት እየተባለ የሚነገርለት አባዱላ ከቀድሞው የኢትዮጵያ ሠራዊት ተማርኮ በሻዕቢያ ፈቃድና በህወሓት ፈጣሪነት አዲስ ስብዕና ተሰጥቶት ኦህዴድ የሚባል የጀመረ መሆኑ የሚዘነጋ አይደለም። ይህ ስብዕናው ህወሓት በህንፍሽፍሽ ልትበታተን ስትል የኦሮሞውን ክንፍ ይዞ መለስን የታደገ በመሆኑ ባለውለታነቱ ለማን እንደሆነ በድጋሚ ያስመሰከረ ሆኗል።

በሌላው አንጻር አባዱላ የኦሮሚያ ዋና ኃላፊ በነበረበት ጊዜ ጁነዲን ሳዶ በኦሮሚያ የፈጠረውን ካቢኔ እና አደረጃጀት በማፍረስ አዲስ ለመለመላቸው የኦህዴድ አባላት “አትደግፉን ነገር ግን የክልሉን ልማት አታደናቅፉ” በማለት እስከ ቀበሌ የደረሰ አዲስ የካድሬ አደረጃጀት አዋቅሮ ነበር። አባዱላ ይህንን ተፈጻሚ ሲያደርግ የሄደበት የአደረጃጀት መንገድ የኦነግም ሆነ የተቀናቃኝ ፓርቲ አባላትን የኦህዴድ ጭምብል በማልበስ ነበር። ለዚህ ድፍረት ያበቃውም በህንፍሽፍሹ የነ ስዬና ተወልደን ውህዳን ቡድን በመቃወም ከመለስ ጋር በመወገን ኦህዴድን ለህወሓት በማዳኑ ከመለስ በተሰጠው “በኦሮሚያ ያሻህን አድርግ” ፈቃድ ነበር። ለካድሬው “ነጻነት” በመስጠት የተወዳጀው አባዱላ ባንድ ወገን ይህ ድርጊቱ የካድሬውን ፍቅር ሲቸረውና “ጃርሳው” ሲያስብለው በሌላው ግን ከአላሙዲ ጋር በግብር ጉዳይ፤ ከመለስ ጋር ደግሞ በተወዳጅነት ቅንዓት ጥርስ ውስጥ አስገባው። እንደ ሰይጣን ወዳጅ የሌለው ህወሓትም አባዱላን አፈጉባኤ በማለት አከሸፈው።

አንድ የማይካድ ሐቅ ቢኖር አባዱላ ኦሮሚያን ከለቀቀ ወዲህ ኦሮሚያ እንደቀድሞው መሆን አቅቷታል። የጁነዲን አርሲ ተኮር ኦህዴድ በጃርሳው ከተናደ በኋላ ኦህአዴድም እንደ ድርጅት የህወሓት ሎሌነቱን በበላይ አመራሩ ብቻ ወስኖ የመካከለኛውና የበታቹ ከከዳ ሰንብቷል። በሙክታር ከዲር የሥልጣን ዘመን ከመለስ ሞት ጋር ተዳምሮ ህልውና ያጣውን ኦህዴድን ወደነበረበት የመመለስ ሥራ የለማ መገርሳ ትከሻ የማይሸከመው ሆኗል።

የመናገር፣ የመጻፍ፣ ሃሳብን የመግለጽ፣ ወዘተ መብቶች በማይታሰቡባት ኢትዮጵያ እንደ ብአዴን በህወሓት ተጠፍጥፎ የተሠራው ኦህዴድና ከስም እስከ ስብዕና ተለክቶ የተሰጠው አባዱላ በቴሌቪዥን ቀርቦ “ሥልጣኔን እለቃለሁ” ብሎ በነጻነት መናገሩ አእምሮ ላለው “እንዴት” ብሎ እንዲጠይቅ የሚያስገድድ ተግባር ነው። በአደባባይ “ስኳር እወዳለሁ፤ ይጣፍጠኛል” አስብሎና አዋርዶ አብሮ የታገለውን ታምራት ላይኔን ያዋረደው ህወሓት፤ በርካታ “በቁምሳጥን ውስጥ የተደበቁ አጽሞች” ያሉበትን አባዱላ ለዚህ “ዕድል” ማብቃቱ ከአባዱላ የመልቀቂ ጥያቄ በላይ በሰበር ዜናነት ሊበሰር የሚገባው ነበር።

ለማንኛውም ሁኔታው በቅርቡ ግልጽ ይሆናል። የኦሮሚያ ጉዳይ እጅግ መከራ ውስጥ ያስገባው ህወሓት አባዱላን በጃርሳውነት ወደ ኦሮሚያ (ጨፌ) ይመልሰው ይሆናል (ከአፈጉባኤነት እንጂ ከድርጅቴ አለቀኩም ማለቱን ያጤኗል) ወይም በቅርቡ በሙስና ጉዳይ ተጠርጣሪ ከአገር እንዲስኮበልል አድርጓል፣ አንጃ ሆኗል፣ በሙስና ተጨማልቋል፣ … ብሎ ወደ ሸቤ ይወረውረዋል። አለበለዚያም ፋይሉ እንደ ተዘጋ ጉዳይ በመዝገብ ቤት በኩል ወደ “ዴድ ፋይል” ክፍል ይልከዋል። ከዚህ ይልቅ ኢትዮጵያን እንደ አገር ለመቆየት የሚያሰጋት በርካታ ጉዳይ መኖሩን ሳንዘነጋ ጥይታችንን በእንደዚህ ዓይነት አናሳ ዜና ላይ ከማባከን ይልቅ በህወሓት ላይ ማድረጉ ነጻነታችንን ቅርብ ያደርግልናል።

ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ታዛቢው ነኝ ከታላቋ እስርቤት ኢትዮጵያ (አዲሳባ) (ፎቶ፡ በተለምዶ አባዱላ የሚባለው ቶዮታ ሚኒባስ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    October 11, 2017 03:00 am at 3:00 am

    ወደ ሸቤ ነው!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ፍፁም ብርሃኔና ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ዋሉ April 16, 2021 10:06 am
  • “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ April 16, 2021 08:45 am
  • “ተዋግተን አይደለም ስንተኛ ብንውል እንኳን መቀሌና አዲስ አበባ አይገቡም” ጄኔራል ባጫ April 14, 2021 09:06 am
  • የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ April 14, 2021 08:53 am
  • “ኤርትራዊ ነን” በማለት የመኖሪያ ፈቃድ ሲቀበሉ የኖሩ የትግራይ ሰዎችን መለየት ተጀመረ April 1, 2021 02:01 am
  • ምርጫ ቦርድ የኦነግን ጥያቄ ውድቅ አደረገ April 1, 2021 01:15 am
  • “እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ April 1, 2021 01:09 am
  • መንግሥት ካልደረሰልን አሁንም ግድያ ይኖራል – ነዋሪዎች April 1, 2021 01:04 am
  • በትግራይ ሊዘረፍ የነበረ የእርዳታ እህል ተያዘ April 1, 2021 12:39 am
  • “በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አልደራደርም” March 24, 2021 01:22 am
  • “ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ March 23, 2021 11:28 pm
  • እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ March 23, 2021 10:23 pm
  • በርግጥ ኢትዮጵያ ዝናብ አዝንባለች? March 23, 2021 10:15 pm
  • አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች March 21, 2021 08:57 pm
  • ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ March 19, 2021 04:32 pm
  • ባልደራስና የአብን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ March 18, 2021 01:56 pm
  • ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም” March 17, 2021 09:54 pm
  • በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ነው – የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት March 17, 2021 04:54 am
  • ምርጫ ቦርድ ከፈቀደለት ኦነግ በምርጫው እንደሚወዳደር አስታወቀ March 17, 2021 04:30 am
  • በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው March 15, 2021 11:25 am
  • በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ March 15, 2021 10:13 am
  • የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ March 15, 2021 09:26 am
  • በትግራይ ትምህርት ቤቶች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ March 15, 2021 09:04 am
  • በማይካድራ የጅምላ መቃብር ተገኘ፤ በህወሓት የተገደሉት ቁጥር ከ1300 እንደሚበልጥ ተነገረ March 15, 2021 08:54 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule