በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ገርጂ አካባቢ በቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ስራ ተቋራጭነት በMH ኢንጅነሪንግ አማካሪነት እየተገነባ የሚገኘው ብሔራዊ ስታዲየም በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተገነባ ይገኛል። የስታዲየሙን የጣራ እና የማጠቃለያ ግንባታ የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢፊድሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር እንዳሉት በሀገራችን የነበረው ብቸኛው ስታዲየም የአዲስ አበባ ስታዲየም እንደነበር ጠቁመው በአሁኑ ሰዓት በሁሉም የሀገራችን ክልሎች ከ12 በላይ ስታዲየሞች በመገንባት ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል። እነዚህ ስታዲየሞች ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ አስፈላጊው ክትትል እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪም መንግስት ለስፖርት ሴክተር በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት በከፍተኛ … [Read more...] about የአደይ አበባ ብሔራዊ ስታዲየም የጣራና የማጠቃለያ ግንባታ በይፋ ተጀመረ