በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሰጡት ማብራሪያ ዋና ዋና ነጥቦች‼️ የምክር ቤት አባላቱ ፦- የስምምነቱ ሂደት እንደምታውና ፋይዳው ምንድነው ?- በጦርነቱ የተጐዱ አካባቢዎችን ፍትሃዊ በሆነ መልኩ የመልሶ ለመገንባት ምን ዝግጅት ተደርጓል ?- አንዳንዶቹ ስምምነቱ ከTPLF እንጂ ከTDF ጋር አይደለም ? ... ወዘተ የሚሉ የተለያዩ ሃሳቦችን እየሠነዘሩ ይገኛሉ ፤ የእነኚህ አካላት ፍላጎት ምንድን ነው ? ውሳኔዎችንስ ተግባራዊ ለማድረግ እነቅፋት አይሆንም ወይ?- የምክክር ኮሚሽን የእስካሁኑ አፈፃፀም ያለበት ደረጃ እንዲሁም በውይይት ሂደቱ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ምቹ ሁኔታዎችና ስጋቶች ምንድን ናቸው?- ውይይቱ ተሳክቶ መላው የሀገራችን ሕዝቦች ወደ ሚናፍቁት ልማት ፊታቸውን እንዲያዞሩ ከባለድርሻ አካላት ማለትም ከምሁራ፣ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ወጣቶችና ከመላው … [Read more...] about በፓርላማው ውሎ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሾች
abiy ahmed
በአራዳ ክፍለ ከተማ ዜጎች የስፖርት ሜዳ አገኙ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ በአዲስ መልክ የተገነባውን የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራ መርቀው ከፍተዋል። በተለምዶ "15 ሜዳ" ተብሎ የሚጠራው የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፋራ ከዚህ ቀደም ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ ምቹ እንዳልነበር ተጠቁሟል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አነሳሽነት የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ በአዲስ መልኩ ተገንበቶ በመጠናቀቁ በዛሬው ዕለት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል። የስፖርት ማዘውተሪያው ግንባታ ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ በሚያመች መልኩ የተገነባ በመሆኑ የቀደመ አግልግሎቶቹን እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራው ግንባታ የክረምት በጎ ፈቃድ ፕሮጀክት አካል መሆኑም ተገልጿል። (አዲስ ማለዳ) በዘመነ ት ህነግ አዲስ አበባ ውስጥ ወጣቶች ምንም ዓይነት … [Read more...] about በአራዳ ክፍለ ከተማ ዜጎች የስፖርት ሜዳ አገኙ
“ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ
ዛሬ በተካሄደው የእንደራሴዎች ምክርቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። ከጥያቄዎቹ የሚከተሉት ነበሩ፤ 👉የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ከትምህርት ምዘና ይልቅ ፖለቲካዊ ቅርጽ እየያዘ አገራዊ አደጋ እየሆነ መጥቷል፤ ፈተናውን ኦንላይን ለመስጠት ምን ታስቧል፤👉 የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከአገር አልፎ ለአፍሪካ ኩራት የሆነ የተመሰከረለት ሰራዊት ነው፤ ለዓለም ሰላም ዋጋ ከፍሏል፤ ነገር ግን ዓለም ይሄንን ውለታ ክዷል፤👉 ምዕራባዊያን ከኢትዮጵያ ጠላቶች ጎን ቆመዋል፤ በውስጥ ጉዳያችን ጣልቃ ገብተዋል፤ ይህ ለምን ይሆናል?👉 የሱዳን መንግስት ዜጎቻችንን ከሚጨፈጭፉ ቡድኖች ጋር ይተባበራል፤ ትእግስትም ልክ አለውና መንግስት የሱዳንን ወረራና ትንኮስ እንዴት እያየው ነው፤ በሲቃ ውስጥ ላሉ ለታፈኑ የትግራይ ዜጎች መንግስት ምን እገዛ እያደረገ ነው፤ ምን … [Read more...] about “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ
አረንጓዴ ቢጫ እና ቀዩ ሰንደቅ የአፍሪካዊያን የነጻነት ምልክት ነው
አፍሪካዊያን አያቶቻችን የደረሰባቸው ውርደት በእኛ ምድር ላይ አይደገምም ከሚሊዮኖች ደህንነት ይልቅ የግል ስልጣናቸው በሚያስጨንቃቸው ግለሰቦች በሰጡት የተሳሳተ መረጃ የተነሳ ለሚፈጠርብን ጫና አንበረከክም፤ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን መስከረረም 17 ቀን 2014ዓም ግልጽ ደብዳቤ ጽፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ደብዳቤያቸው አሸባሪው ህወሓት እንደ አገር ያደረሳቸውን ግፎችና በደሎች ዘርዝረው አስረድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ደብዳቤያቸውም ህወሓት እንደ አገር በፈጸማቸው ግፎችና ወንጀሎች የተነሳ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሸባሪ ቡድን ብሎ እንደፈረጀው በማስታወስ፤ ይህ ቡድን በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈጸም በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት መጀመሩን ጠቅሰዋል። ከዚህ ጦርነት በኋላም ይህ አሸባሪ ቡድን በአፋር … [Read more...] about አረንጓዴ ቢጫ እና ቀዩ ሰንደቅ የአፍሪካዊያን የነጻነት ምልክት ነው
“ለዶሮ በሽታ በሬ ማረድ ትክክል አይደለም” ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ
አንዳንዶች ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ በቆዩበት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነት የመጨረሻ ዘመንና የመጨረሻው ሳምንት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ሰኔ 28 ቀን 2013. ዓ.ም. በነበራቸው ጥያቄና መልስ፣ በአገሪቱ ታሪክ ከፍተኛ የተባለውን 561 ቢሊዮን ብር የ2014 ዓመታዊ በጀት እንዲሆን የቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ በሙሉ ድምፅ በማፅደቅ የመጨረሻ የውሳኔ አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡ በዕለቱ ከፍተኛ የአገሪቱ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ መሪዎች፣ የግሉ ዘርፍ ተወካዮችና ሌሎችም አካላት በተገኙበት በዚሁ የፓርላማው ስድስተኛ ዓመት አራተኛ ልዩ ስብሰባ በወቅታዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ያመዘኑ በርከት ያሉ ጥያቄዎች ከ15 የምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀርበውላቸው ነበር፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምክር ቤቱን … [Read more...] about “ለዶሮ በሽታ በሬ ማረድ ትክክል አይደለም” ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ
“መቀሌን ከሽሬ ወይም ከበሻሻ የሚለያት የስበት ማዕከል የለም”
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ ከትናንት በስቲያ አመሻሹን ከጋዜጠኞች ጋር ተገናኝተው ነበር። ሚዲያው በምርጫው ላደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለማመስገን በተዘጋጀው በዚህ መርሀ ግብር ላይም ሚዲያውን ካመሰገኑ በኋላ ስለ ምርጫው እና ስለ ትግራይ ሁኔታ ለጋዜጠኞች አብራርተዋል። ካነሷቸው ነጥቦች መሀከልም የተወሰኑትን በግርድፍ እንዲህ አስታውሻቸዋለሁ በምርጫው እኛም ሆነ ተቃዋሚዎች የተመኘነውን ያህል ቡራቡሬ ፓርላማ አላገኘንም! ተቃዋሚዎች በምርጫው ውጤት ደስተኛ ባይሆኑም በምርጫ ቦርድ፥ በፍርድ ቤት እና በሚዲያ ላይ ቅሬታ እንደሌላቸው ተስማምተናል! ሚዲያው የትርክት ለውጥ ላይ በደንብ መስራት አለበት። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ከዚህም በላይ መስበክ አለበት! በትግራይ ባካሄድነው ዘመቻ ተይዘውብን የነበሩትን መሳሪያዎች በሙሉ አስመልሰናል። ማስተካከል የምንፈልገውንም … [Read more...] about “መቀሌን ከሽሬ ወይም ከበሻሻ የሚለያት የስበት ማዕከል የለም”
ምዕራባውያን – “ለድርድር እናስገድዳለን ካልሆነ ወደ ዶ/ር ዐቢይ እንዞራለን”
ይህ ድምፅ የምዕራባውያኑ የመጨረሻው ድምፅ ነው። ወስነዋል። የመጨረሻውን ጫና ጀምረዋል። ጫናው እየጨመረ ይሄዳል። ለምን በአዲስ መልክ ጫናውን ጀመሩ ብንል ተስፋ አድርገውት የነበረው የተመድ የፀጥታው ም/ቤት እነሱ እንደሚፈልጉት ባለመወሰኑ ይመስላል። በክፍል 3 የመጨረሻ ካርዶችን እንይ:-1ኛ) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን ዶክተር አብይ ጋር ደውሎ ነበር። በትግራይ ረሃብ ሊከሰት ስለሚችል ያሳስበኛል። በሃገሪቱ ያለው የብሄር ውጥረቶችም ያሳስበኛል። የኤርትራ ጦር ይውጣ። ሁሉም አካላት ጦርነት አቁመው ወደ ድርድር መምጣት አለባቸው። ወዘተ የሚል ውይይት አድርጓል። የዚህ ስልክ አላማ በአጭሩ ከሞተው ጁንታ ጋር "ድርድር እና እርቅ" አድርግ የሚል ነው። ካልሆነ ግን (የብሄር ውጥረቶች ያልኩህ ሌላ መልክ እንዲይዙ እናደርጋለን። እርስበርስ ትፋጃላችሁ። ከዚያም አልቻልክም ተብለህ … [Read more...] about ምዕራባውያን – “ለድርድር እናስገድዳለን ካልሆነ ወደ ዶ/ር ዐቢይ እንዞራለን”
“በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አልደራደርም”
“ተላላኪ መንግስት አይኖርም” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለበርካታ ዓመታት የነጮ ተላላኪ በመሆን ያገለገለው እና ሞት እንደ ቡሽ ክዳን ያስፈነጠረው መለስ ዜናዊ በግፍ ኢትዮጵያን በገዛበትና ከዚያ በኋላ ባሉት ዓመታት ፈጽሞ ባልተሰማ ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለአገራቸው ያላቸውን ስሜት በግልጽ ተናግረዋል። ኢትዮጵያን ተቀጥሮ እንደሚያስተዳድራት መሪ “አገሪቱ” እያለ ሲጠራት ከኖረው መለስ ዜናዊ በኋላ ፍጹም በተጻረረና ልብን በሚያሞቅ የአገር ስሜትና ወኔ ከእንግዲህ በኢትዮያ ተላላኪ መንግሥት እንደማይኖር ነው ለሕዝባቸው በፓርላማው ውይይት የተናገሩት። የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ “በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አይደረግም” ሲሉ ተጽዕኖ ለማሳደር ለሚሞክሩ አካላት ተናግረዋል። ዛሬ (ማክሰኞ) ለፓርላማ ባቀረቡት ንግግር … [Read more...] about “በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አልደራደርም”
“ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
ዛሬ (ማክሰኞ) በተካሄደው 5ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሰጡት ማብራሪያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፤ የኢኮኖሚው አጠቃላይ ገጽታ፤ የፍኖተ ብልጽግና እቅዳችን ያለፉትን 3 አመታት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው፤የአገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም መሰረታዊ አጀንዳዎቻችንየብድር ጫና መቀነስተጀምረው የቀሩ በርካታ ፕሮጀክቶች በፈጠነ መንገድ ማጠናቀቅየወጪ ንግዱን ማሻሻልና ማሳደግገቢን ማሻሻልገበያን ማረጋጋትና የዕድገት ቀጣይነትን ማረጋገጥ፤የህዳሴ ግድብ በነበረበት ችግር ምክንያት የአገር ኢኮኖሚ እግሩ ተፈትቶ መሄድ እንዳይቻል አድርጎ ነበር፤የወጪ ንግድም ትልቅ ችግር ውስጥ ነበር፤ ባለፈው አመት ለመጀመሪያ ገፊዜ መሻሻል አሳይቷል፤እነዚህን አጀንዳ ስንቀርጽ ኮቪድ … [Read more...] about “ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው”
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በመቀሌ ከከፍተኛ የጦር መኮንኖች ጋር ተወያዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሕግ ማስከበር ሂደቱን ከመሩ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ጋር መቀሌ ላይ ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በአካባቢው ለሕዝቡ እየተደረገ ያለው ሠብዓዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። መቀሌ ላይ በተካሄደው ውይይት ጄኔራል አበባው ታደሰና ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ተሳትፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መሆኑን በውይይቱ ላይ ተናግረዋል። በጁንታው ላይ የተገኘው ድል የሚያኩራራ ሳይሆን 'የምንማርበትና የኢትዮጵያን ቀጣይነት የምናረጋግጥበት ነው' ማለታቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የትግራይን ክልል መልሶ ለማቋቋም መንግስት … [Read more...] about ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው”