• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመለስ “ሌጋሲ” በአዜብ መታገድ መቃብር ገባ

November 28, 2017 02:43 am by Editor 4 Comments

  • ህወሓትን ለመምራት ደብረጽዮን፣ ዓለም፣ ጌታቸውና ፈትለወርቅ ታጭተዋል

እርስበርሱ ሲነታረክ የቆየው የህወሓት ግምገማ አባይ ወልዱን በማባረርና አዜብ መስፍንን በማገድ እርምጃ መውሰዱ ታውቋል። እነደብረጽዮን የሚመሩት የማጽዳት ዘመቻ በመለስ “ሌጋሲ” ላይ አብሮ እርምጃ ወስዷል። የመሪነቱን ቦታ ፈትለወርቅ፣ ደብረጽዮን፣ ጌታቸውና ዓለም እየተፎካከሩበት ነው ተብሏል።

አፍቃሪ ህወሓትና የህወሓት ልሳን ከሆኑ የዜና ምንጮች በቀረበው መረጃ መሠረት ሰሞኑን በግምገማ እርስበርሱ ሊበላላ ደርሶ የነበረው የህወሓት ግምገማ “ቆራጥ” እርምጃዎችን ወስዷል። በዚህም መሠረት በመለስ ዜናዊ ምትክ የ“ወንበዴ” ድርጅቱ ኃላፊ ሆኖ ሲሠራ የነበረው አባይ ወልዱ ከሊቀመንበርና ሌሎች ከፍተኛ ኃላፊነቶች ተወግዶ በተራ አባልነት እንዲቀጥል ተወስኖበታል።

ከአባይ መሰናበት በተጨማሪ “አዜብን መንካት የመለስ ሌጋሲን አደጋ ላይ መጣል ነው” በሚል እንድምታ በግዱ ለአዜብ ሲያጎነብስ የነበረው ትግራይን ለመገንጠል የተቋቋመው ቡድን አዜብን ከከፍተኛ ኃላፊነቷ አንስቷታል። ከቀናት በፊት አዜብንና ተላላኪዎቿን ለመቀርጠፍ ግምገማው ሲጣደፍ በነበረበት ጊዜ አዜብ መስፍን ስብሰባውን ረግጣ መውጣቷ ይታወቃል። ለዚህ ድርጊቷ በተደጋጋሚ ይቅርታ ብትጠይቅም ሆነ ደብዳቤ ጽፋ ብታስገባም “ኃጢአቷን ካናዘዘ” በኋላ በዕገዳው ጸንቷል።

“ባለራዕዩ መሪ” እየተባለ ሲሞገስና ሲሞካሽ የኖረው መለስ በሙት መንፈስ አገሪቱን ሲመራ መቆየቱ የሚታወቅ ነው። ሞት እንደ ቡሽ ክዳን በድንገት ቢያስፈነጥረውም ህወሓት በእርሱ መንፈስ እመራለሁ ሲል አዜብም “አንዲት ሓሳብ ይዞ ወደ ምድር” የመጣውን ሙት ባሏን ከለላ በማድረግ ያሻትን ስትናገርና ስትከውን ላለፉት አምስት ዓመታት ቆይታለች።

መለስ ከመሞቱ 3ዓመት በፊት በአሜሪካ ከአውሮጵላን ለመውረድ ሲችገር

በህወሓት ነባር ወንበዴዎች ዘንድ በንቀት የምትታየው አዜብ ከመለስ ሞት በኋላ ከማንኛውም ኃላፊነት እንድትወገድ ሲሞከር ቆይቷል። ሆኖም እርሷን በሙስና ወይም በሌላ ሰበብ ማባረር በመለስ ውርስ (ሌጋሲ) ላይ ትልቅ ጥያቄ ያስነሳል በሚል ውሳኔው ተግባራዊ ሳይደረግ ቆይቷል። በሙስና ከተባረረች የሙስናው እፍታ ለመለስም ደርሷል የሚለው አስተሳሰብ የባለራዕዩን መሪ ስም የሚያጠለሽ ነው የሚል አስተያየት ሲሰጥበት ቆይቷል። በኪራይ ሰብሳቢነት ወይም በችሎታ፣ በአቅም ማነስ ወይም በአስተሳሰብ ደካማነት ወይም በሥልጣን መባለግ በሚሉ ሰበቦች ብትባረር ያለ ችሎታዋና ያለ አቅሟ ወደ ሥልጣን እንድትመጣ ያደረገውን መለስ አሁንም የሚያዋርድ ነው በሚል ጥርስ ሲነከስባት ሰንብቷል።

በህወሓት ጉዳይ ውስጥ አዋቂ ነን የሚሉ እንደሚናገሩት አዜብ መታገድ ብቻ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ከድርጅቱ ትባረራለች የሚል አስተያየት እየሰጡ ናቸው። ይህ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ከእርሷ ጋር አብሮ የመለስ ሌጋሲ በዜሮ እንዳባዛ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት ያሳስባሉ። በመሆኑም እስካሁን የአዜብን ጉዳይ በትዕግስት ሲያስታምም የቆየው ህወሓት አዜብ የምትባረረው ከመለስ ሞት በኋላ በፈጸመችው ስህተት መሆኑን በማጉላት የመለስን “ሌጋሲ” ለማዳን የፕሮፓጋንዳ ሥራ የመሥራት ዕቅድ ያስፈልጋል የሚሉ ወያኔዎች የሚሰጡት አስተያየት አብላጫነት እያገኘ መጥቷል።

አዜብን በማገድ፣ በየነ ምክሩንና አባይ ወልዱን በማባረር የቀጠለው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) ግምገማ በተባረሩት ምትክ አዳዲስ አባላትን ያስገባል። በዓለምአቀፋዊ የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ለተመዘገበው ድርጅት – ህወሓት – መሪ ይመርጣል። ሁለቱ የደኅንነትና የስለላ ማሽኖች ደብረጽዮን ገብረሚካኤልና ጌታቸው አሰፋ እንዲሁም ዓለም ገብረዋህድ ለመሪነት ቀዳሚ ተፎካካሪዎች እንደሆኑ የህወሓት ተላላኪዎች ቢናገሩም በበረሃ ስሟ “ሞንጆርኖ” እየተባለች የምትጠራው ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ቀጣይዋ የህወሓት መሪ እንደምትሆን ስዩም ተሾመ ምንጮቼ አረጋግጠውልኛል በማለት በፌስቡክ ገጹ ላይ ዘግቧል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Alem says

    November 28, 2017 06:53 pm at 6:53 pm

    ውድ ጎልጉል፣
    የሚያሳዝነው፣ ህወሓት በአገራችን ዕጣ ብቸኛ ወሳኝ ሆኖ የሚያካሄደውን ስብሰባ ሌላው እንደ ተመጽዋች እጁን አጣምሮ መጠባበቁ ነው። ዛሬ ደግሞ አፍቃሬ ወያኔው ሪፖርተር፣ ምሑራን ወደ ኤርትራ ሄደው ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እንዲያደርጉ ህወሓት መፍቀዱን ገልጿል። ምሑራኑን የሚመሩት ሀብቶም እና መድሐኔ ናቸው። ትልቅ ቀልድ፣ የሰው ልክ የማያውቅ መንግሥት ገጥሞናል። የሥልጣን ጥመኛውና ሥራፈቱ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ደግሞ የኢትዮጵያ ደመኛ ኢሳይያስ የሥልጣን ኮርቻ ላይ ያፈናጥጠኛል ብሎ ተስፋ አድርጓል። ከሌንጮ ለታ፣ ከታምራት ላይኔ እንኳ መማር አልቻለም። ዶ/ር ብርሃኑ በ97 ምርጫ ህዝብ ተገልብጦ ወጥቶ እርሱ ግን ፈርጥጦ ከአገር ወጣ። ህወሓት ወዲያው የተበተነውን ወጣት ለቃቅሞ ኪሱ ከተተ። ከዚያን ወዲህ “ተቃዋሚ” ገለመሌ የሚለው ቋንቋ ወጣቱን ቋቅ ብሎታል። የህወሓት ጥንካሬ የኛ ዝርክርክነትና ዓለማ ቢስነት ግልባጭ ነው። ሌላው አሳዛኝ ጉዳይ የድረገጾች የውሸት ናዳና ተስፋ ነው። ህወሓት ሊወድቅ ነው! ምሥጢሩን ይዘናል! የውሸት ተስፈኞች አድርጎናል። ስንት ዓመት ይህን ስንሰማ ኖርን፤ አንዱም እውን አልሆነም። እናንተ ግን ጎልጉላችሁ እውነቱን ከመናገር ችላ አትበሉ።

    Reply
    • Editor says

      November 29, 2017 09:30 am at 9:30 am

      ሰላም Alem

      ለላኩልን መልዕክት እናመሰግናለን።

      በተለይ “… ዛሬ ደግሞ አፍቃሬ ወያኔው ሪፖርተር፣ ምሑራን ወደ ኤርትራ ሄደው ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እንዲያደርጉ ህወሓት መፍቀዱን ገልጿል። ምሑራኑን የሚመሩት ሀብቶም እና መድሐኔ ናቸው …” ባሉት ጉዳይ ላይ እየሠራንበት ነው በቀጣይ የምናቀርበው የዜና ዘገባ ይሆናል።

      ከአክብሮት ሰላምታ ጋር

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    November 28, 2017 10:48 pm at 10:48 pm

    አይ ዓዜብ!ዓዜብ!የመለስ ሚስት! ዓዜብ!
    ልክሰስሽ!? አሁን!?ሰው እስኪታዘብ?
    ላዋርድሽ!? ቂሊንጦ ላስገባሽ?ላስጠብቅሽ በዘብ?

    አየሽ! ዓዜብ!ዓዜብ!
    ላሸክምሽ! የውርደትሽን ቀለብ?
    ባልሽና አንቺ ከጠላት ወግኖ መረባረብ?
    እሱ ሲሞት አንቺ በማደብ!
    በመደበቅ! ዱካ አጥፍቶ መረባረብ?
    ልክተትሽ?ከሴ?ዓዜብ?

    ነውር ነው!! በስርቆት ተለክፈሽ!
    ይባስ ብለሽ አይናውጣ ሆነሽ!እኔን ልታጠፊ ሞክረሽ!
    ልክተትሽ? በተራ ስርቆት ላስገባሽ?
    ውነት ቅን ነበር ባልሽ?
    እኛን ጨፍልቆ አንቺን ሲያሻሽ!
    በስርቆት ወንጀል ላስገባሽ?
    እስቲ ማን ዋቢ ይሁንሽ?
    ቢቀር ቢቀር ስድስት ወር ታጪያለሽ?
    ነውር ነው! ነውር ነው! ያንቺና የባልሽ!
    መልስ ስጪኝና ላሳይሽ!
    ተቀመጪ ቅሌት ተከናንበሽ!
    ዓዜብ! ዓዜብ!አበቃልሽ!የተራ እንኳን አባልነትሽ!
    ዕድሜ ለሃይለ ማርያም ብለሽ!
    ተቀመጪ ከእንግዲህ በቃሽ!!
    ከእንግዲህ ስልጣን አይመርሽ!!

    Reply
  3. dergu temelese says

    November 29, 2017 11:07 am at 11:07 am

    የቀን ገቢው ሚሊዮን፣
    የወር ገቢው ቢሊዮን፣
    ከጫካ ሲመጣ ያልነበረው ስሙኒ፣
    ዛሬ ባለ ካምፓኒ፣
    ሎተሪ ያልወጣለት ውርስ የሌለው፣
    ይህን ሰው ማን ዕንበለው?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule