Note: Ethiopia is a current non-permanent member of UN security council and a member of UN human rights council VOA Interview: Part-1 (23 March 2017) + Part-2 (25 March 2017): Habtamu Ayalew: Former spokesman of Andenet Party (Ethiopia) VOA Introducer, Alula Kebede: Today’s guest for democracy in action program is Mr. Habtamu Ayalew, former spokesperson of the opposition, Andenet Party (unity party) in Ethiopia. Mr. Habtamu was subjected to two years of imprisonment, waiting for trial after … [Read more...] about Horrifying Testimony of Torture in TPLF Prison: Ethiopia
Politics
የብአዴን መክዳትና የ“በቀል” ፍርሃት የወለደው “የኢኮኖሚ አብዮት” በኦሮሚያ፤
“ህወሃት የፈጸመው ግፍ በየትኛውም ዘመን የሚረሳ አይሆንም” በህወሃት ገደብ የለሽ የሥልጣን ፍቅርና የቁስ ሰቀቀን ውልቅልቋ እየወጣ ያለችው ኢትዮጵያ ከፍታው ርቋት የቁልቁለቱን ጉዞ ተያይዛዋለች። ለወጣበት ዘውግ ልዕልና የሚተጋው ህወሃት ህግና ሞራል በማይዳኘው ድርጅታዊ ቀኖናው እየተመራ ኢትዮጵያን ማድማቱን ቀጥሎበታል። እስር፣ ቶርቸር፣ ስቃይ፣ ስደት፣ ሞትና የግዞት ኑሮ ከህወሃት ዘውግ ጥላ ውጪ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እድል ፈንታ ሆኗል። ከነዚህ በመከራ ከሚዳክረው የኢትዮጵያ ሕዝብ መካከል አንዱ የኦሮሞ ሕዝብ ነው። እውነታው ግን ሰፊና ለም የሆነ መሬት ላይ የሰፈረው የኦሮሞ ሕዝብ በቁመቱ ልክ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱ ሊከበርለት እንዳልቻለ ወራሪው ህወሃት ራሱ ለፖለቲካ ፍጆታም ቢሆን ያመነውና ማንም ሊከደው የማይችል የአደባባይ ሃቅ ነው። በአገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ላይ … [Read more...] about የብአዴን መክዳትና የ“በቀል” ፍርሃት የወለደው “የኢኮኖሚ አብዮት” በኦሮሚያ፤
በህወሃት የታፈነው ድርቅ ወደ ረሃብ እያደገ ነው፤ ት/ቤቶች ተዘግተዋል!
የኢትዮጵያ ሶማሌ ዘጠኙም ዞኖች ሙሉ በሙሉ የድርቁ ሰለባ ሆነዋል! በክልሉ 437 የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ከድርቁ ጋር በተያያዘ ተዘግተዋል፤ 183,090 ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠዋል! የእርስበርስ ዕልቂት ያሰጋል! የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በሁለት ወራት ውስጥ ባወጣቸው ተከታታይ ሪፖርቶች ምስራቅ አፍሪካ የከፋ ድርቅ መከሰቱንና ዓለም የዕርዳታ እጆቹን ለአገራቱ እንዲዘረጋ በተከታታይ ሪፖርቶቹ ተማጽኗል፡፡ እንደ በዘገባው ከሆነ ድርቁ የከፋባቸው ተጠቃሽ አገራት ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኬንያና ኢትዮጵያ ናቸው፡፡ ከኢትዮጵያ ውጭ የተጠቀሱት መንግሥታት ለዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ የዕርዳታ እጃቸውን በመዘርጋት፤ በተባበሩት መንግሥታት በኩል የአውሮጳ ህብረትና ሌሎች ለጋሾች በከፋ ድርቅ ላይ ለሚገኙት አገራት ዕርዳታ እየሰጡ ናቸው፡፡ በተባበሩት መንግስታት … [Read more...] about በህወሃት የታፈነው ድርቅ ወደ ረሃብ እያደገ ነው፤ ት/ቤቶች ተዘግተዋል!
አድዋን ወደ ፖለቲካ ድል መቀየር ለምን ተሳነን? እርግማን ሦስት “ምኒልክ የእኛ ነው”
ከዝግጅት ክፍሉ:- “አድዋን የሚያህል ወታደራዊ ድል ስለምን ወደ ፖለቲካዊ ድል መቀየር ተሳነን?” በሚል ርዕስ ተከታታ ጽሁፎች ስናትም ሰንብተናል፡፡ የመጀመሪያው ክፍል ሙሉ ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡ እርግማን ሁለት “ሚኒልክ ኤርትራን ሸጠ፤ ትግራይን በደለ” የሚለው ሁለተኛው ክፍል ደግሞ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ በሦስተኛው ክፍል የመጨረሻውንና ማጠቃለያውን ይዘን ቀርበናል፡፡ አፄ ምኒልክ ባልዋለበት ማዋል የዘመናችን “ፖለቲከኞች” ከታሪክ የሚያገኙት ግብር - አልባ ትርፍ ሆኗል፡፡ የአፄውን አገር የማቅናትና የግዛት አንድነትን የማስከበር ዘመቻ በ“ቅኝ ግዛት” የሚተረጉሙት እንዳሉ ሁሉ የማዕከላዊ መንግስት መቀመጫ ከትግራይ ወደ ሸዋ በመዞሩ ምኒልክን “ባንዳ” እና “አገር ሻጭ” እያሉ የአባቶቻቸውን ዝንፈት በአደባባይ ምኒልክ ላይ የሚለጥፉ ብልጣብልጥ “ፖለቲከኞች” … [Read more...] about አድዋን ወደ ፖለቲካ ድል መቀየር ለምን ተሳነን? እርግማን ሦስት “ምኒልክ የእኛ ነው”
አድዋን ወደ ፖለቲካ ድል መቀየር ለምን ተሳነን? እርግማን ሁለት: “ምኒልክ ኤርትራን ሸጠ፤ ትግራይን በደለ”
ከዝግጅት ክፍሉ:- "አድዋን የሚያህል ወታደራዊ ድል ስለምን ወደ ፖለቲካዊ ድል መቀየር ተሳነን?" በሚል ርዕስ የመጀመሪያውን ክፍል ማቅረባችን ይታወሳል፤ ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህኛው ክፍል ሁለት ዕትም እርግማን ሁለት “ሚኒልክ ኤርትራን ሸጠ፤ ትግራይን በደለ” የሚለው ርዕስ ዳሰናል፡፡ የኢትዮጵያ አገራዊነት ታሪክ ተፃሪሪ ትርጓሜና የዘመናዊት ኢትዮጵያ አገር ምስረታ ሂደት የተመዘዙ መንታ ሰበዝ ናቸው፡፡ “ቅኝ ግዛት” vs “አገር ምስረታ፣ ማቅናት/ግንባታ” የሚሉ ተፃራኒ ትርጓሜዎች እንዳሉ ሁሉ፤ “አገር ሻጭ” እና “ባንዳ” የሚሉ የፖለቲካ እርግማኖች የዘመናዊት የኢትዮጵያ የታሪክ ገጽታ አካል ሆነው ቀርበዋል፡፡ ማንነትን የታከከ የታሪክ ትርጓሜ ባለበት ሁኔታ እነዚህ ብያኔዎች ሊጠፉ የማይችሉ የታሪክ ፍም እሳቶች ናቸው፡፡ በዚህም የተነሳ በገዥዉ ኃይል ፊት … [Read more...] about አድዋን ወደ ፖለቲካ ድል መቀየር ለምን ተሳነን? እርግማን ሁለት: “ምኒልክ ኤርትራን ሸጠ፤ ትግራይን በደለ”
አድዋን የመሰለ ወታደራዊ ድል ስለምን ወደ ፖለቲካዊ ድል መቀየር ተሳነን?
እንደ መግቢያ በታወቀ ምክንያት የኢትዮጵያ ታሪክ አወዛጋቢነት ቀጥሏል፡፡ “ታሪክ የሞተ ፖለቲካ ነው” የሚለው አባባል ለእኛ ለኢትዮጵያዊያን አይሰራም፡፡ ይልቁንስ “ታሪክ የነበረ፣ ያለና ወደፊትም ሊቀጥል የሚችል ፖለቲካ ነው” በስሜት በሚነዳ የዘውግ (የዘር፣ የጎሣ) ፖለቲካ ውስጥ ታሪክ ትልቅ ማገዶ ሆኖ ቀርቧል፡፡ እንዲህ ባሉ የታሪክ ውርክቦች ውስጥ ይበልጥ አትራፊው ገዥዉ ኃይል መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ታሪክ የአሸናፊዎች ደንገ-ጡር በሆነችባት ኢትዮጵያ ገዥው ኃይል ለአገዛዙ በሚያመቸው መልኩ ታሪክን በርዞና ከልሶ ሲያቀርብ ታሪክን ሳያላምጡ የሚመጡ ደቃቅ “ፖለቲከኞች” በርክተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ታሪክ አተራረክ በአጥቂነትና በተከላካይነት የሚበየን የውዝግብ መድረክ ሆኗል፡፡ የአንድ ዘውግ ጉዳይን ሁልግዜ በተጠቂ ስሜት፤ ሌላኛውን ዘውግ በአጥቂነት የማየት ዝንባሌም በታሪክ … [Read more...] about አድዋን የመሰለ ወታደራዊ ድል ስለምን ወደ ፖለቲካዊ ድል መቀየር ተሳነን?
“ምኒልክነትን የጠየቀው” የአድዋ ድል!
“ … ወታደር ባለመሆኔ የጦርነቱን ውሎ ማተት አያምርብኝም፡፡ ያም ሆኖ የአድዋ ድል ዛሬ ብርቅ በሆኑብን ሁለት እሴቶች ረድኤት የተገኘ ይመስለኛል፡፡ እኒህ ሁለት እሴቶች መተባበርና መደማመጥ ናቸው፡፡ ጣልያኖቹ በጊዜው ወደ ጦርነት ሲገቡ ተስፋቸውን የጣሉት በመድፍና በጠመንጃቸው ሳይሆን ኢትዮጵያውያን ዝነኛ በነበሩበት የውስጥ መቆራቆስ ላይ ነው፡፡ የትግራይ ቅልጥም ሲመታ ሸዋ ያነክሳል ብለው አላሰቡም፡፡ በርግጥም በክፍለ ሀገሮች ውስጥ የተለያዩ ሽኩቻዎች ነበሩ፡፡ እኒህን ሽኩቻዎች አስረስቶ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ለአንድ አላማ ማሠለፍ ምኒልክነትን ይጠይቃል፡፡ “መደማመጥ ያልሁትን ላሳይ፡፡ አባ ዳኘው ከዛሬው የይስሙላ ፓርላማችን በተሻለ ሁኔታ ለልዩነቶች ቦታ የሚሰጥ ተንቀሳቃሽ ምክር ቤት በጦርነቱ ወቅት መፍጠር ችለዋል፡፡ ፀሐፌ ትእዛዝ ገብረሥላሴ በውጊያው ዋዜማ የነበረውን ሁኔታ እንዲህ … [Read more...] about “ምኒልክነትን የጠየቀው” የአድዋ ድል!
የአለቃ ጸጋየ በርሄና የህላዊ ዮሴፍ ወጎች፤ ከሹመት እስከ ሽረት፤
የህወሓት-እስራኤል ቀጣይ የፖለቲካ ቁማር! አሁን ባለዉ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የኃይል አሰላለፍ ለህወሓት/ኢህአዴግ ቁልፍ የስጋት ምንጩ የዲያስፖራዉ የተቃዉሞ ጎራ ነዉ፡፡ የድህረ-ምርጫ 97 ዉርስ ዕዳ የሆነዉ የዲያስፖራዉ ተጽዕኖ ፈጣሪነት እንደ ሀገር ቤቱ ሁሉ በዘዉግ ፖለቲካ የሚታመስ ቢሆንም በጋራ ጠላት (ህወሓት/ኢህአዴግ) መዉደቅ ላይ ያለ አንዳች የልዩነት መስመር ይስማማል፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ ሀገር ቤት ያሉት የተቃዉሞ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ከሚያሰሙት ጩኅት በላይ ከባህር ማዶ የሚሰማዉ ሹክሹክታ እንቅልፍ ይነሳዋል፡፡ የህዝብ ድምጽና የዲያስፖራዉ የተቃዉሞ ፖለቲካ መሳ ለመሳ መሄድ የቆላ ቁስል ሆኖበታል፡፡ እናም የዲፕሎማሲ ታርጋን እንደ ሴራ ፖለቲካና ድርጅታዊ ጠቀሜታነት አብዝቶ ለመጠቀም የጨዋታዉን ህግ ያሻሻለ ይመስላል፡፡ የዲያስፖራ ፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪነት በማይካድ ደረጃ … [Read more...] about የአለቃ ጸጋየ በርሄና የህላዊ ዮሴፍ ወጎች፤ ከሹመት እስከ ሽረት፤
ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት አለመኖሩን” አመነ
የካቲት 13፣ 2009 ደመቀ መኮንን፣ ገዱ አንዳርጋቸውና የጎንደር ከተማ ከንቲባ ተቀባ ተባባል በአንድነት የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን ባንጋገሩበት ወቅት ገዱ አንዳርጋቸው "መንግሥት የለም" እየተባለ የሚነገረውን የሚያረጋግጥ አስተያየት መስጠቱ ተስማ። እንደ ፋና ዘገባ ከሆነ ከተሰብሳቢው ለደመቀ በርካታ ጥያቄዎች ቀርበውለታል፡፡ ፋና ይፋ ባያደርገውም በውይይቱ የከረሩ ጉዳዮች መነሳታቸው ከአንዳንድ ምንጮች ለመረዳት ተችሏል፡፡ ደመቀ በገለጻው “ጥልቅ ተሃድሶ፤ መልካም አስተዳደር፤ የህዝብ ተሳትፎ፤ ...” በማለት ተሰብሳቢውን ለማሳመን ጥረት ቢያደርግም የተቻለው እንዳልሆነ ፋና ራሱ ከዘገበው ለመረዳት ቻላል፡፡ “... ተሃድሶው አንዱን አመራር ወደ ሌላ ስፍራ ከመቀየር የዘለለ ለውጥ እያመጣ አይደለም” የሚል አስተያየት ከውይይቱ ተሳታፊዎች መነሳቱን የጠቆመው የፋና ዜና ለዚህ ጥያቄ … [Read more...] about ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት አለመኖሩን” አመነ
ወያኔ እንዲህ እያሰበ መሆኑ ጭምጭምታ ተሰማ፤ ዕውነት ከሆነ ጥቅምና ጉዳቱ ምን ይሆን?
ዛሬ ላለንበት ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትንና ዐማራ የተሰኘውን ነገድ ከመኖር ወደ አለመኖር ያደረሳቸውን ምክንያት መገንዘብ፣ ለምንፈልገው መፍትሔ ጥርጊያ መንገድ ይከፍትልናል። ከትግራይ ነፃ አውጭ ግንባር (የትግሬ-ወያኔ) የትግል ጉዞ እንደምንረዳው፣ ችግር በገጠመው ቁጥር፣ ዓላማውንና ቆሜለታለሁ የሚለውን ሥርዓት እንደ እባብ ገላ በሌላ በመተካት ጊዜ ይገዛል። ከማኦ ዜ ዱንግ እስከ ኤንቨር ሆጃ፣ ከካርል ማርክስ እስከ ሌኒን፣ ከሂትለር እስከ ደቡብ አፍሪቃ የአፓርታይድ አገዛዝ ያሉትን ርዕዮተ-ዓለሞች ካንዱ ወደ ሌላው ከብርሃን ፍጥነት በፈጠነ ሁኔታ በመቀያየር ኅልውናውን ለማራዘም ይሞክራል። የትግሬ-ወያኔ ላለፉት 25 ዓመታት ያራመደው በዘር ጥላቻ ላይ የተመሠረተ ፖለቲካና አገሪቱንና ሕዝቡን በነገድ ሸንሽኖ ያደረሰው ጥፋት፣ በተለይ ከ2007 እስከ 2009 ዓም ያሉት ዓመታት ሕዝቡ ሊሸከመው … [Read more...] about ወያኔ እንዲህ እያሰበ መሆኑ ጭምጭምታ ተሰማ፤ ዕውነት ከሆነ ጥቅምና ጉዳቱ ምን ይሆን?