• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሴት ልጅ በሽፍታ እጅ ወድቃ የሚተኛ ጎን የለኝም

January 28, 2020 05:45 am by Editor Leave a Comment

ከሃምሳ ቀናት በላይ በአጋቾች እጅ ያሉት እህቶቻችን ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ሆኖብናል። የአንድ ሃገር ህዝብ ከሁሉ በፊት የሚፈልገው ነገር ዋስትና ነው። ተማሪው፣ ነጋዴው፣ ገበሬው፣ ሰራተኛው ሁሉ ከመንግስት የሚጠብቀው ዋና ነገር ደህንነቱ እንዲረጋገጥለት ነው። የመንግስት ተቀዳሚ ተግባርም ይሄ ነው።

ለውጥ በሃገራችን ጀመረ ካልንበት ማግስት ጀምሮ ከፍተኛ መፈናቀልና አለመረጋጋት ሃገራችንን እየናጣት ነው። ይህንን ችግር የለውጥ ባህርይ ኣድርገን የምናይ ካለን ስህተት ነው። የሰው ደም ሳንገብር ወደ ለውጥ የምናልፍበትን መንገድ ነው የምንሻው እንጂ ከዚህ በፊት በየለውጡ ያየነውን ኣይነት የኢትዮጵያውያን ስቃይ እንዲደገም አንሻም። በመሆኑም የለውጥ መሪዎች ቁጥር አንድ ስራ የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ መሆን ኣለበት።

ከሃምሳ ቀናት በላይ በእገታ ላይ የሚገኙት የሃገር ተስፋ የሆኑ እህቶቼና ወንድሞቼ ህይወት በአንድም በሌላም መልኩ ከመንግስት የጸጥታ አመራር ጋር በቀጥታ የተገናኘ ችግር ነው። ስለሆነም መንግስት ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እነዚህን ወጣቶች የማዳን ስራ መስራት አለበት። ወታደራዊ ጥበቦችና የአመራር ጥበቦች ሁሉ ወደነዚህ ወገኖች ሊያዘነብሉ ይገባል። እኔ እንደገባኝ አጋቹ ታውቋል። ምክንያቱም የጠቅላይ ሚንስትሩ ጽህፈት ቤት ሰክሬታሪያት አቶ ንጉሱ ጥላሁን ሲናገሩ እንደሰማሁት የተለቀቁ ተማሪዎች እንዳሉና ለቀሩት ድርድር እየተደረገ እንደሆነ ገልጸዋል። ይህ ማለት መንግስት ኣጋቹን ኣውቋል ማለት ነው። ስለዚህ እነዚህ እህቶቻችንና ወንድሞቻችንን የማትረፍ ኦፐሬሽን መደረግ ኣለበት። ይህ ኦፐሬሽን በከፍተኛ የሰኪዩሪቲና ወታደራዊ ጥበብ የታገዘ መሆንም አለበት። መረጃዎች ለህብረተሰቡ መገለጽ አለበት።

በተለይ ደግሞ ሴት ልጅ በሽፍታ እጅ ወድቃ የሚተኛ ማህበረሰብ የለንም። ሴት በሽፍታ እጅ ወድቃ እንቅልፍ ኣይኖረንም። የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ሆናችሁ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በተቀናጀ ትግል እነዚህን ሴቶች መታደግ ያስፈልጋል። ይህንን በማድረግ በሃገራችን ቀድሞ የማናውቀውን ይህንን የማገት ጅማሮ ከስሩ መንቀል ኣለብን። ኢትዮጵያችን የቦኮሃራም ዋሻ ልትሆን በምንም ዓይነት ኣንፈቅድም። በመላ ሃገሪቱ የምትገኙ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የብሄር ልዩነትን ጌጥ አድርጋ ሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ቦኮሃራም ቦታ የለህም ማለት አለባችሁ። ለአጠቃላይ የሃገራችን የደህንነት ዋስትና ቆርጣችሁ መነሳት አለባችሁ። የትም ዓለም ቢሆን ዴሞክራሲና መልካም ኣስተዳደር የመጣው በትግል ነው። መንግስት በገፋነው ልክ የሚሄድ ነገር ነውና ለውጡ በሰዎች መጉላላትና ደም ላይ ሳይሆን በሰላምና በአንድነት እንዲቀጥል ንቅናቄዎች ያስፈልጋሉ።

ሴት ልጁ የተነካበት ማህበረሰብ ቀፎው እንደተነካበት ንብ ብድግ ብሎ ሊነሳ ይገባል። ለውጥን የሚመራው ህዝብ ነውና በየጊዜው ለውጡን የሚያስቱ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ ህዝቡ አቅጣጫ የማሳየትና የመታገል ሃላፊነቱን በንቃት ሊወጣ ይገባል።

እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!

ገለታው ዘለቀ (geletawzeleke@gmail.com)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: bring back our sisters, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule