• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በመንግሥታችን ምክንያት አገራችን ተከፋፍላለች” ቴዲ አፍሮ

July 14, 2017 04:12 pm by Editor 2 Comments

  • ቴዲ “የአማራ ሙዚቀኛ በመሆን ቀጥሏል” ዘ ጋርዲያን
  • “ወቅቱ አደገኛ ነው፤ አሁን እኔ ቅድሚያ የምሰጠው ለኢትዮጵያ ነው” ቴዲ

የፍቅር፣ የዕርቅና አንድነትን መልዕክት በማንገብ ዘፈን ዘፍኖ ገንዘብ ከመሰብሰብና ታዋቂ ከመሆን በላይ የሚለፋው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አዲሱ አልበሙ ከወጣ በኋላ ከእንግሊዙ ጋዜጣ ዘ ጋርዲያን ጋር ባደረገው ቃለምልልስ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ቁልጭ አድርጎ ተናግሯል፡፡ “በመንግሥታችን ምክንያት አገራችን ተከፋፍላለች” ያለው ቴዲ “የአፍሪካ ሞዴል ነበርን” በማለትም የቀደመውን የኢትዮጵያን ታላቅነትና ክብር አስታውሷል፡፡

በቅርብ የተለቀቀውን “ኢትዮጵያ” አልበም በተመለከተና ስለ አገሩ እንዲሁም ስለ ራሱ የህይወት ፍልስፍና የዜና ዘገባ ያወጣው ዘ ጋርዲያን ቃለ ምልልሱን ያደረገው በቴዲ የመኖሪያ ቤት በመገኘት ነበር፡፡ ስለ ቴዲ የቀድሞ ሥራዎች፣ ሰው ገጭተህ ገድለሃል በሚል ክስ ተመሥርቶበት በእስር ስላሳለፈው ህይወቱ፣ አዲሱ አልበሙ በሽያጭ ቀዳሚነትን የያዘ ስለመሆኑ ወዘተ በርካታ ጉዳዮችን በዘገባው አካትቷል፡፡

“ወጣቱ ትውልድ ያለፈውን ታሪኩን በተመለከተ አጣብቂኝ ውስጥ ነው ያለው፤ (የአገራችንን) መልካም ታሪክ የማስተማር ኃላፊነት እንዳለብኝ ይሰማኛል፤ (ወጣቱ) ስላለፈው ታሪክ ስኬት ኩራት ሊሰማው ይገባል” በማለት የተናገረው ቴዎድሮስ ካሳሁን አዲሱ አልበሙ ይህንኑ የኢትዮጵያን የቀድሞ ገናናነት እንደገና በማስታወስ ለአንድነት ጥሪ የሚያደርግ ሥራ መሆኑን ተናግሯል፡፡

በእነዚህና ሌሎች የቴዲ ሥራዎች ላይ ጋዜጣው ትንታኔ ከሰጠ በኋላ ኢትዮጵያን ለመከፋፈል የኖረ ምኞት እንዳላቸው አውሮጳውያን አቅጣጫውን በመቀየር ቴዲ አፍሮን ከአጼ ቴዎድሮስ፣ ምኒልክና ኃይለሥላሴ ጋር በአንድ የዘር ቋት ውስጥ መድቦ ሲያበቃ ሁሉንም አማራ በማለት ከመሰየም አልፎ ቴዲንም የአማራ ብሔረተኝነትን ናፋቂ አድርጎ አቅርቦታል፡፡ ለዚህ አስተሳሰቡ ደጋፊ ማስረጃ ለማድረግም በቴዲ ክፍሎች ውስጥ የምኒልክ ጎራዴ፣ የኃይለሥላሴ ዘመን ሠንደቅ ዓላማና የሳቸው ፎቶ መኖሩን አብሮ አስፍሯል፡፡ ለዚህ መሰሉ ፍረጃ ቴዲ የሰጠው መልስ “ወጣቱ ትውልድ አባቶቹ ለዚህች አገር ምን እንዳደረጉ ማወቅ አለበት፤ ምኒልክ ለዚህች አገር፣ ለአንድነት እና ለጸረ ቅኝአገዛዝ መዋጋታቸው ግልጽ ነው” በማለት ኢትዮጵያዊ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ዓላማ ይዞ የተነሳ የሚመስለው ጋዜጣ ግን ኢትዮጵያ ውስጥ 88 ቋንቋዎች የሚነገሩ ቢሆንም ቴዲ ግን “የአማራ ሙዚቀኛ በመሆን ቀጥሏል” በማለት ቴዲን በዘር ሣጥን ውስጥ ከቶታል፡፡ በመቀጠልም “ከታዋቂዋ የአማራ ድምጻዊት ሒሩት በቀለ” ጉልበቶች ላይ ቁጭ ብሎ እሷ ስትዘፍን ያዳምጥ እንደ ነበር ማስታወሱን ዘግቧል፡፡ ይህ የጋዜጣው ዘገባ አገላለጽ የቀደሙትንም ሆነ አዲሶቹን የኢትዮጵያ ድምጻዊንን በህወሓት/ኢህአዴግ የዘር መስፈሪያ ውስጥ አስገብቶ ለማጥበብ የሞከረ ሆኖ ማግኘታቸውን ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ገልጸዋል፡፡

ጋዜጣው በማጠቃለያው የቴዲ ሙዚቃ ቅንብሮች ከኢትዮጵያና ከዳያስፖራው ባለፈ መልኩ በዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የማይሰሙ መሆናቸውን ከገለጸ በኋላ ምክንያቱንም ሲያስረዳ ቋንቋውም ሆነ የሙዚቃው ስልት ኢትዮጵያዊ በመሆኑ ነው ብሏል፡፡ ከዚህ አልፎም ቴዲን ከሙላቱ አስታጥቄና መሐሙድ አህመድ ጋር በማነጻጸር የቴዲ ሥራዎች እንደ ሁለቱ አርቲስቶች ለምዕራባውያን አድማጮች ቅቡል አለመሆናቸውን ላነሳው ሃሳብ እንደ ተጨማሪ ማድመቂያ አቅርቧል፡፡ ለዚህ ግን የቴዲ ምላሽ “ወቅቱ አደገኛ ነው፤ አሁን እኔ ቅድሚያ የምሰጠው ለኢትዮጵያ ነው” ብሏል፡፡

እንደ ሃሳብ፤ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ቴዎድሮስ ካሳሁን ኢትዮጵያዊ ድምጻዊ እንደሆነ ያምናል፡፡ በዚህ የ “ዘ ጋርዲያን” ዘገባ ላይ ቴዲን የአማራ አርቲስት ተድርጎ የቀረበው ሃተታ አግባብነት አለው ብለን አናምንም፡፡ የቴዲ አፍሮ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ለዚህ የተዛባ አቀራረብ ማስተካከያ ይሆን ዘንድ በተለይ ለ “ዘ ጋርዲያን” ምላሽ ቢሰጥ ሃሳብ እናቀርባለን፡፡ (Photograph: Mulugeta Ayene AP)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    July 15, 2017 04:17 pm at 4:17 pm

    ውድ ጎልጉል፣ ቶም ለተሰኘ ለ”ዘ ጋርድያን” ጸሐፊ ሁለት ጊዜ ማብራርያ ጽፌ ሁለቱንም ጊዜ ሠርዞታል። የመጀመሪያ ቅሬታዬ በሙዚቃው ዓለም ጥላሁንን አለማንሳት አይቻልም የሚል ነው። ሁለተኛው የአገራችንን ታሪክ አለማወቁ መሐሙድ አማራ ሙዚቀኛ አይደለም፤ በአማርኛ ግን ይዘፍናል። በትግርኛ ቢዘፍን አድማጭ 100 ሺህ ሰው አይሞላም [ከትግራይ 4 ሚሊዮን ሕዝብ ሁሉም ሬዲዮ አለው ሁሉም ያደምጣል ካላልን በስተቀር]። በወላይትኛም፣ ወዘተ። አማርኛ ብዙ ሰው የሚሰማው ስለሆነ፣ ከገበያም አንጻር። በበአንጻሩ ዴጃቩ እና አባዲ ለተባሉት ሠፊ መድረክ ሰጥቶአቸዋል። ለ ዘ ጋርድያን ዋና አርታኢ ቅሬታ ማቅረብ ይኖርብናል።

    Reply
    • Editor says

      July 15, 2017 04:57 pm at 4:57 pm

      መልካም ብለዋል አለም። ሌሎችም የርስዎን አርአያነት ቢከተሉ የሚበጅ ይመስለናል። ከሁሉ በላይ ግን የቴዲ አፍሮ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ጋዜጣውን ቢያነጋግር የተሻለ መፍትሔ ያመጣል ብለን እናምናለን።

      ጊዜዎን ወስደው ስለላኩልን አስተያየት እናመሰግናለን።

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ፍፁም ብርሃኔና ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ዋሉ April 16, 2021 10:06 am
  • “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ April 16, 2021 08:45 am
  • “ተዋግተን አይደለም ስንተኛ ብንውል እንኳን መቀሌና አዲስ አበባ አይገቡም” ጄኔራል ባጫ April 14, 2021 09:06 am
  • የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ April 14, 2021 08:53 am
  • “ኤርትራዊ ነን” በማለት የመኖሪያ ፈቃድ ሲቀበሉ የኖሩ የትግራይ ሰዎችን መለየት ተጀመረ April 1, 2021 02:01 am
  • ምርጫ ቦርድ የኦነግን ጥያቄ ውድቅ አደረገ April 1, 2021 01:15 am
  • “እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ April 1, 2021 01:09 am
  • መንግሥት ካልደረሰልን አሁንም ግድያ ይኖራል – ነዋሪዎች April 1, 2021 01:04 am
  • በትግራይ ሊዘረፍ የነበረ የእርዳታ እህል ተያዘ April 1, 2021 12:39 am
  • “በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አልደራደርም” March 24, 2021 01:22 am
  • “ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ March 23, 2021 11:28 pm
  • እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ March 23, 2021 10:23 pm
  • በርግጥ ኢትዮጵያ ዝናብ አዝንባለች? March 23, 2021 10:15 pm
  • አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች March 21, 2021 08:57 pm
  • ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ March 19, 2021 04:32 pm
  • ባልደራስና የአብን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ March 18, 2021 01:56 pm
  • ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም” March 17, 2021 09:54 pm
  • በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ነው – የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት March 17, 2021 04:54 am
  • ምርጫ ቦርድ ከፈቀደለት ኦነግ በምርጫው እንደሚወዳደር አስታወቀ March 17, 2021 04:30 am
  • በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው March 15, 2021 11:25 am
  • በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ March 15, 2021 10:13 am
  • የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ March 15, 2021 09:26 am
  • በትግራይ ትምህርት ቤቶች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ March 15, 2021 09:04 am
  • በማይካድራ የጅምላ መቃብር ተገኘ፤ በህወሓት የተገደሉት ቁጥር ከ1300 እንደሚበልጥ ተነገረ March 15, 2021 08:54 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule