ፈጣሪ በየትውልዱ የራሱን ድምጽ ያወጣልፍቅር ያሸንፋል-- የኔ ሳይሆን የትውልድ ድምጽ ነውእዳ አለ የምንል ከሆነም፤ እዳ የሚከፈለውና የሚሸፈነው በፍቅር ብቻ ነው የፍቅር ጉዞ ከሚለው ሃሳብ እንጀምር፡፡ መነሻው ምንድነው? “አቦጊዳ ብዬ፣ ፊደል “ሀ”ን ቆጥሬ፤ የፍቅርን ትርጉም ለልቤ አስተምሬ፣ ይዤሽ በአኮፋዳ እንደቆሎ ተማሪ፣ አቦጊዳ ልበል የፍቅር ጀማሪ…” እንዲህ ነው የኔ የዘፈን ህይወት የሚጀምረው። አሁን የፍቅር ጉዞ ላይ ደርሷል፡፡ ሁላችንም፣ በተለያዩ የታሪክ አጋጣሚዎች ውስጥ እናልፋለን። ብዙ ቅሬታና ብዙ ደስታ፣ ብዙ ትክክል የሆኑ ነገሮችና ብዙ ትክክል ያልሆኑ ነገሮች አሉበት - ያለፍንበት ታሪክ፡፡ ትልቁ ነጥብ፣ ካለፍንበት ታሪክ ተነስተን ለሚቀጥለው ጊዜ ምን እናድርግ የሚለው ነው፡፡ ያዘንበትን ነገር በይቅርታ ሰርዘን፣ የወደድነውን ነገር ደግሞ አሳድገን … [Read more...] about “ከወረስነው ቂም ይልቅ የምናወርሰው ፍቅር ይበልጣል”
የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር ወጣቱ ትውልድ ራሱን ከፅንፈኞች ማራቅ ታሪካዊ ግዴታው ነው !
ከጠባቦችና የግንጠላ አራማጆቸ ጎራ እንደሚስተጋባው ከንቱ ታሪክ አገራችን ኢትዮጵያ በድንገት የዛሬ መቶ አመት የተከሰተች ሳይሆን በብዙ ዘመናት የዜጎች መስዋዕትነት የተገነባች አገር ናት። ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ ለማድረግ የብዙ ሚሊዮንና የአያሌ ትውልድ ኢትዮጵያውያን ህይወት ተገብሮባታል። ይነሰም ይብዛም፣ ይጉላ ይደብዝዝ፣ ሁሉም ህዝብ ለዚያች አገር ግንባታ አሰተዋፅኦ አድርጉአል። በሌሎች አገሮች ታሪክም እንደተከሰተው ሁሉ በኢትዮጵያም ታሪክ ጦርነት የሀገር ግንባታው ሂደት አካል ሆኖ ተገኝቷል። በሂደቱ ለጠፋው ህይወትና ለደረሰው በደል የዛሬው ትውልድ ከቶም ተጠያቂ ሊሆን አይችልም ብሎ ኢወክንድ ያምናል። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር ወጣቱ ትውልድ ራሱን ከፅንፈኞች ማራቅ ታሪካዊ ግዴታው ነው !
ወገንን በመርዳት ለኢትዮጵያ ያለን ፍቅር ይገለጻል!
የዶክተር ካትሪን ሃምሊን እና የባለቤታቸው በዶ/ር ሬጅ ሃምሊን ግማሽ ክፍለ ዘመን የተጠጋው በጎ ምግባር የሚያሳዩ ድርሳናትን ስፈታትሽ አድሬ አረፋፈድኩበት ። "የፊስቱላ ተጠቂዎች የተስፋ ታሪክ " በሚል በአንድ ወቅት በፊሱትላ በሽታና በዶክተር ካትሪን እና በቤተሰባቸው በስራ ባልደረቦቻቸው ተጋድሎ ዙሪያ የቀረበ በእጀ ነበረ ከሲድኒ አውስትራልያ መስፍን ማሞ ተሰማ ያቀረበልንን ድንቅ በበቂ መረጃ ደጋግሜ አነበብኩት። "ዶ/ር ካትሪን ሀምለን በአሁን ሰአት በአውስትርሊያ ግዛት በአንድ የባህር ዳርቻ በሚገኘው ምቾታማና የናጠጠ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ቀሪውን የህይወት ዘመናቸውን እንኳ ለማሳለፍ አልፈለጉም። ዛሬም በዚህ እድሜያቸው ከሃገር ሃገር እየዞሩና እየተንከራተቱ ዕርዳታ በመጠየቅ የፊስቱላን በሽታ ከምድረ ኢትዮጵያ ለማስወገድ እንዲቻል የፋይናንስ፤ የማቴሪያልና የባለሙያ ኃይልን እያደራጁ … [Read more...] about ወገንን በመርዳት ለኢትዮጵያ ያለን ፍቅር ይገለጻል!
“Time to bring back Eritrea from the cold”
Many observers agree that recent unfortunate developments in the Middle East can easily spillover to the Greater Horn of Africa region2. There are groups that are fanning ideologies advanced by the various actors in Middle East’s sectarian conflict. In the light of the new developments in the region, it makes sense for the United States to review its relationship with Eritrea and Ethiopia and rebalance its portfolio. The interesting question for Eritrea and Ethiopia is therefore how to respond … [Read more...] about “Time to bring back Eritrea from the cold”
ዜጋዊ ጥያቄ
የካቶሊክ “ቤተክርስቲያን” በሀገራችን የራሷን ዩኒቨርስቲ ልትከፍት ነው በግንባታ ላይ ይገኛል፡፡ ስለ ጉዳዩ ምን ታስባላቹህ ? ይህ ነገር ከኢትዮጵያዊነትና ከብሔራዊ ጥቅም አንጻር በረከት ነው ወይስ መርገም ? በነገራችን ላይ ዩኒቨርስቲውን በሀገራችን ለምን እንደሚከፍቱት ታውቃላቹህ ? የካቶሊክ “ቤተክርስቲያን” ከመጀመሪያው ጀምሮ በሀገራችንና በሕዝቡ ላይ የነበራትንና ያላትን ጥቅምና ፍላጎት ታውቃላቹህ ? የካቶሊክ “ቤተክርስቲያን” አስቀድሞ በታሪካችን ያደረገችውን ታውቃላቹህ ? የካቶሊክ “ቤተክርስቲያን” አስቀድሞ ከረጅም ጊዜና ከአጭር ጊዜ ዐቅድ አንጻር ጥቅሟን የሚያሳካላት ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ለሀገራችን ያደረገችው አንድም የመልካም ሥራ ዝጋብ (ሬከርድ) እንደሌለ ታውቃላቹህ ? የካቶሊክ “ቤተክርስቲያን” ፋሺስት ጣሊያን ሀገራችንን በወረረ ጊዜ እጇን በቀጥታ … [Read more...] about ዜጋዊ ጥያቄ
ህ.ወ.ሓ.ት. የኢ.ሕ.አ.ፓ. አመራርና ሌሎች ታጋዮች የጦር ምርከኞች በጅምላ ረሽኖ በትራክተር አፈር መልሶባቸው እንደቀበራቸው
ይህንን አሳዛኝና ዘግናኝ ዜና "ኢትዮሚዱያ" በመባል የሚታወቀው ድህረ ገጽ ላይ በጀነዋሪ 2014 ዓ.ም. ወጥቶ አንብቤአለሁ:: ህወሓት በኢ.ሕ.አ.ፓ አመራርና ላልች ታጋዮች የጦር ምርከኞችን በጅምላ ረሽኖ በትራክተር አፈር ተመልሶባቸው እንዲቀበሩ ማድረጉን ኢትዮሚዲያ አስነብቦናል:: ህወሓት ከዚህ የበለጠ ብዙ ዘግናኝና አሰቃቂ ድርጊቶችን በሌሎች ኢትዮጵያውያን ላይ እየፈፀመ እንንሆነ አስተርጓሚ የሚያሻው አይደለም:: (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ህ.ወ.ሓ.ት. የኢ.ሕ.አ.ፓ. አመራርና ሌሎች ታጋዮች የጦር ምርከኞች በጅምላ ረሽኖ በትራክተር አፈር መልሶባቸው እንደቀበራቸው
The Ethiopians and their past
We love to visit the past. There is no one like us that digs deeper, travel further to harvest the bounty of our rich past. To say we dwell on the past is definitely an understatement. I would not be surprised if scientists after mapping our brain find a special pocket where we store ugly little tidbits of the past to fuel our anger. To claim we live in the past is not far from the truth. Compared to others what makes our situation a little different is how we use the past to explain or … [Read more...] about The Ethiopians and their past
ፕሮፌሰሩ – ሰክነው ማዳመጥ ለሚችሉ መናገር ያስደስታቸዋል
ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የኢትዮጵያ ሶሻል ፓርቲና የደቡብ ህብረት ፓርቲ መሪ ናቸው። በግል የመድረክ መስራች ሲሆኑ፣ የሚመሩት ድርጅትም በመድረክ ጥላ ስር ከተሰባሰቡት ፖለቲካ ድርጅቶች መካከል ይገኝበታል። ፕ/ር በየነን ጨምሮ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ኢህአዴግን በመቃወም የሚታወቁ ፖለቲከኞች ተተኪ ፖለቲከኞች አላዘጋጁም በሚል ይወቀሳሉ። በዚህ ጉዳይ ስማቸው ከሚነሱት መካከል አንዱ ፕ/ር በየነ ናቸው። ፕ/ር በየነ አሜሪካ ለሥራ መምጣታቸውን ተከትሎ የጎልጉል ዘጋቢ ቃለ ምልልስ አድርጎላቸዋል። ፕ/ር በየነ በቃለ ምልልሳቸው ወቅት በተደጋጋሚ "እኔ የምናገረው ሰክነው ማዳመጥ ለሚችሉት ነው" በማለት ያሳስባሉ። ለምን? ጎልጉል፡- ስለ መንግሥትና ተቃዋሚዎች እርቅ ጉዳይ ወሬ ይወራል የሰሙት ነገር አለ? ፕ/ር በየነ፡- የለም። ምንም አልሰማሁም። ጎልጉል፡- እርስዎ የሚመሩት ፓርቲ ጥያቄው … [Read more...] about ፕሮፌሰሩ – ሰክነው ማዳመጥ ለሚችሉ መናገር ያስደስታቸዋል
ርዕዮት አለሙ ጋዜጠኛ እንጅ አሸባሪ ናት ብየ አላምንም!
የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን ስራዎች በቅርብ ተከታትያለሁ! ውንጀላ እስራቷን ፣ ህክምና እንድታገኝ መደረጓን እና የቤተሰብ እና የወዳጆችዋ ጉብኝት እንዳታገኝ መከልከሏን ሰምቻለሁ ! ይህ ሁሉ በዚህች የመናገር የመጻፍ ነጻነቷን ተጠቅማ ህገ መንግስታዊ መብቷን በተጠቀመች ወጣት ጋዜጠኛ ላይ የሚከፈል መስዋዕትነት ቢሆንም ስቃይ መከራዋ ፣ በደል መገፋቷ ያንገበግበኛል!እናም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ተተገፈፈቸው መብቷ ይመለስ ዘንድ በሚደረገው ሰላማዊ እንቅስቃሴ ደጋፊ ነኝ ! ርዕዮት አሸባሪ አይደለችም ብየ አምናለሁና ፊርማየን ለድጋፍ ሳስቀምጥ ኩራት ይሰማኛል ! ፍትህ ለጋዜጠኛ ርዕዮትና ለመሰሎቿ ስመኝ ለኢትዮጵያስ እንኳንም ተወለድሽ የምላት አሁንም በኩራት ነው! ግጥሙን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ:: … [Read more...] about ርዕዮት አለሙ ጋዜጠኛ እንጅ አሸባሪ ናት ብየ አላምንም!
“ወደው አይስቁ”
የጥምቀት በዓልን ተሰባስበን በምናከብርበት አንድ ቤት ውስጥ ካለወትሮው ፓልቶክ ተከፍቷል። በዚያ የበዓል ድባብ፤ የፓልቶክ ንትርክ መከፈቱ ሳይገርመን፣ ርእሱ የሁላችንንም ቀልብ መሳቡ። በእርግጥ አንድም ቁም ነገር በንግግሩ አልሰማንም። አዲሱን ቋንቋ ልዋስና የፓልቶኩ ተናጋሪዎች ሙድ የሚያስይዙ ነበሩ። ሰዎቹ በዚህ ከቀጠሉ የእነ ክበበው ገዳን ገበያ መዝጋት እንደሚችሉ አያጠራጥርም። የድምጽ መነጋገርያውን የያዘው ሰው ጉሮሮውን ጠራርጎ ንግግሩን እንዲህ ሲል ጀመረ። "የምኒሊክ ወንጀል በጡት መቁረጥ ብቻ አያበቃም። ... የወንዶች ብልትም ተቆርጧል።..." በአኖሌ ሃውልት የምትገረሙ ነፍጠኞች ካላችሁ። በዚህ ብዙም አትደነቁ። ገና የወንድ ልጅ ሃፍረተ-ስጋ በሃውልት መልክ በአደባባይ ይቆምላችኋል። "የባሰ አታምጣ!" ነው ነገሩ። ሜንጫዎቹ ሰክረዋል። አእምሮዋቸውም ስቷል። የሚናገሩትን … [Read more...] about “ወደው አይስቁ”