አልሸባብ ጋልሙዱግ በሚባል ክልል ከሶማሌ ጦር ጋር ባደረገው ውጊያ ሶስት የሶማሊያ ጦር ካምፖችን በቁጥጥሩ ስር አድርጓል። አል ሸባብ ከሶማሊያ ጦር ጋር አምስት ሰዓታት ያህል የቆየ ከባድ ጦርነት ካካሄደ በኋላ ከጥቃቱ የተረፉ የሶማሌ ብሄራዊ ጦር የ"ጎርጎር ኮማንዶ" መኮንኖችና ወታደሮች እንደተናገሩት በውጊያው ከ230 በላይ የሶማሊያ ወታደሮች መሞታቸውን እንዳረጋገጡና ስፍር ቁጥር የሌላቸው መቁሰላቸውን ገልፀዋል። የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር በቦታው ያሰፈራቸው ወታደሮቹ 4 ሻለቃ የ"ጎርጎር ኮማንዶዎችን" ሲሆን 15 የአል ሸባብ አሸባሪዎች ጋር ባደረገው ውጊያ ከፍተኛ ሞትና የአካል ጉዳት አስተናግዷል።የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር በአል ሸባብ ከበባ ውስጥ ሆኖ ምንም ዓይነት የሽፋን ኃይል ማሰማራት አልተቻለውም ተብሏል።ፕሬዝደንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በአል ሸባብ የሽብር ቡድን ላይ … [Read more...] about አል ሸባብ ሦስት የሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ካምፖችን ተቆጣጠረ
የተዘቀዘቀ መስቀል?!
“አርቲስት ቴዲ አፍሮ የጥምቀት በዓልን ወደ አደባባይ ወጥቶ ማክበሩን የሚያሳይ ፎቶ ተለቋል” ሲሉ ነው በርካቶች ባሰራጩት አስተያየት “ነገሩ ምንድን ነው?” ሲሉ ግራ በመጋባት ማብራሪያ የጠየቁ ቢበዙም፣ ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊት ፈጽመው የነበሩ አካላት ላይ ውግዘት መድረሱን ያስታወሱም አልታጡም። የሚያደርገውን በማወቅ፣ ጊዜና ሰዓት በማስላት በሚያከናውናቸው ተግባሮቹ ስኬት የለኩት “ቴዲ ሳያውቅ ይህን ለበሰ ለማለት ያስቸግራል” ሲሉም ተድምጠዋል። የዲዛይን ችሎታ አካታ እንዳያዘች የሚነገርላት ባለቤቱ አምለሰት ሙጬ በጥንቃቄ እንደምትሞሽረው የሚያውቁ “ይህን እንደ ስህተት መቀበል ያዳግታል” ሲሉ አስቸኳይ ማብራሪያ እንደሚሹ አመልክተዋል። ፎቶውን በማጋራት ሰፋ ያለ አስተያት ከጻፉት መካከል ቶማስ ጃጃው በቴሌግራም ገጹ “እንደ ማንኛውም በብርሃነ ጥምቀቱ እንደሚያምን … [Read more...] about የተዘቀዘቀ መስቀል?!
ፑንትላንድ ለኢትዮጵያ ወደብ በነጻ እሰጣለሁ አለች
የሶማሊላንድና አሜሪካ የጦር ሰፈር ስምምነት ያደርጋሉ ከሶማሊያ ራሷን ለይታ በራስ ገዝነት የምትተዳደረዋ ፑንትላንድ “ኢትዮጵያ የባህር ዳርቻዎቼን አልምታ መጠቀም ትችላለች፤ እኛ በየትኛውም ኢትዮጵያ ወጪ ገቢ ላይ ምንም ዓይነት ቀረጥ አንጥልም” ስትል በባለስልጣኗ አማካይነት መናገሯ ጫጫታ አስነሳ። የሶማሊላንድ መሪ ወደ አረብ ኢምሬትስና አሜሪካ አቅንተው ከፍተኛ የተባለ የጦር ሰፈር ግንባታ ውል እንደሚፈራረሙ ታውቋል። ፑንትላንድ በምታሳያቸው እንቅስቃሴ ክፉኛ ያናደዳቸው የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ለፑንትላንድ መንግሥት የማስጠንቀቂያ መልዕክት ልከዋል። የሶማሌላንድንና የፑንትላንድን አካቶ ይቅርና መቀመጫቸውን ያለ ድጋፍ ማስተዳደር ያልቻሉት ሀሰን ሼክ ኢትዮጵያን ጨምሮ ዛቻ ሲያሰሙ በርካቶችን እያስገረመ ነው። የፑንትላንድ ፕሬዚዳንት ቀጣይ ሳምንት በሚያከብሩት በዓለ … [Read more...] about ፑንትላንድ ለኢትዮጵያ ወደብ በነጻ እሰጣለሁ አለች
የኢትዮጵያን የወደብ ጥያቄ ለማምከን በሶማሊያ የተዘጋጀ ስትራቴጂክ ሰነድ
ሶማሊያ በኢትዮጵያ ላይ በወታደራዊ፣ በዲፕሎማሲ እና በሌሎችም ዘመቻዎች የምትከተለውን ስትራቴጂ የተመለከተው ሰነድ ሚስጥራዊ ማስታወሻ ለ፡ ሐሰን ሼክ ሞሃሙ፣ የሶማሊያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት A confidential Memorandum To: HE. Hassan Sheikh Mohamoud President of the Somali Federal Republic ከ፡ ሙክታር አይናሼ፣ የሶማሊያ መንግሰት የፀጥታ እና የፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኝና አማካሪ፣ የሶማሊያ ዜጋ --ግልባጭ፡ -ሃምዛ ባሬ፣ የሶማሊያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር -አብዲ ሃሺ አብዱላሂ፣ የላዕላይ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ -አደም መሀመድ ኑር ማዶቤ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ፤ እና -ለሁሉም የፌዴራል አባል ክልሎች ፕሬዚዳንቶች ቀን፡ … [Read more...] about የኢትዮጵያን የወደብ ጥያቄ ለማምከን በሶማሊያ የተዘጋጀ ስትራቴጂክ ሰነድ
የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ
በአንድ ጊዜ 8ሺ ሰው በአንድ ቀን ደግሞ እስከ 40ሺ ሰው የሚስተናገድበት ትልቅ የድግስ አዳራሽ በአዲስ አበባ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ከ120 አመት በፊት ሲሠራ የነበረው የምህንድስና፣ ቅርጽና ይዘት፣ የመንግሥታዊ ድግሡ ታዳሚዎች ማንነትና የግብሩ ሥርአት፣ “ቀድሞም ጠቢብ ነበር ሰለሞን አባቱምኒልክ ይበልጣል ሰው ይዞ መብላቱ” ዳግማዊ ምኒልክ ሰዉ ሁሉ አንድ ጊዜ ተሰብስቦ የሚበላበትን ትልቅ አዳራሽ ለመስራት በመወሰን፣ በ1889 ዓ.ም ክረምቱን መናገሻ ወርደው እንጨት ሲያስጠርቡ ከረሙ፡፡ ወታደሩም በድግስ ጊዜ ሜዳ ላይ ሆነን ጸሀይና ዝናብ እንዳይመታን ለኛ ብለው አይደለምን በማለት ደስ ተሰኘ፡፡ ላዳራሹ የሚያስፈልገውን 4 ማዕዘን፣ ሳንቃና እንጨትም ላሊ እየወጣና እየዘፈነ ማመላለስ ጀመረ፡፡ በ1890 ዓ.ም በዘመነ ማርቆስ ዳግማዊ ምኒልክ ከአውሮፓ መሀንዲሶችን … [Read more...] about የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ
የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ
በ116ኛው የሠራዊት ቀን ሲከበር ንግግር ያደረጉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ “ዐጼ ምኒልክ የጦር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ያቋቋሙበትን ቀን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን ኾኖ እንዲከበር ተደርጓል” በማለት ቀኑ ለምን እንደተመረጠ ይፋ አደረጉ። ከዚህ ሌላ ፊልድ ማርሻሉ በንግግራቸው፤ ሉዓላዊነቷ ተጠብቆ ከጀግኖች የተረከብናትን ኢትዮጵያ እንደተከበረች እና ማንነቷ እንደተጠበቀ ለማስቀጠል ወታደራዊ ዝግጁነታችንን አሳድገንና ቁመናችንን አዘምነን ማንኛውንም ተልዕኮ በላቀ ብቃት ለመፈጸም ሠራዊቱ ዝግጁ መሆኑን አሣውቀዋል። የሠራዊቱ አባላት የተሠጣቸውን ታላቅ አደራ በድል ለመወጣት የመፈጸም ብቃታቸውን በማሣደግ በዓላማ ጽናታቸው እንዲቀጥሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አሳስበዋል፡፡ ሠራዊቱ ሀገሩን እና ህገ መንግስታዊ ሥርዓቱን … [Read more...] about የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ
ጥቅምት 15 ለምን?
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቀን በአዲስ መልክ ጥቅምት 15 ቀን ላይ መከበሩ ለምን እንደሆነ ከዚህ በታች ለመረዳት እንዲቻል በቀላሉ የተሠራውን መግለጫ ይመልከቱ። ስለ ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት የማዕረግ ምልክቶች ምን ያህል ያውቃሉ? ከ"ፊልድ ማርሻል ጄነራል" ጀምሮ እስከ "ምክትል አስር ዓለቃ" ድረስ በአጠቃላይ 18 ማዕረጎች ይገኛሉ። የማዕረጎቹን ዝርዝር ከነምልክቱ እነሆ፦ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ጥቅምት 15 ለምን?
“በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት”
"በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት " በሚል መሪ ቃል ለሚከበረው ለዘንድሮ ለ116ኛው የሠራዊት ቀን እንኳን በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን። እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ የረዥም ዓመታት ሀገርን ከጠላት የመከላከል የተጋድሎ ታሪክ ካላቸው ሀገራት መካከል በጀግኖች ልጆቿ የአይበገሬነት ፊት የምትሠለፍ ታሪካዊት ሀገር ናት። ከቀደመው ዘመን ጀምረን አሁን ላይ ያለውን እውነታ እንኳ ብንቃኝ ኢትዮጵያ በርካታ የውጪ ወራሪ ሀገራት ያሠፈሠፉባት ጥቂት የማይባሉ የውስጥ እርስ በርስ ግጭቶች የተከሰቱባት በባንዳዎች የተፈተነችበትና በየትኛውም ዘመን ያልተንበረከከች የወራሪዎችን ፈተና አልፋ ዛሬ ላይ የደረሠች ሥለመሆኗ የታሪክ ድርሳናት መዝግቧል። በሀገራችን የጀግንነት የታሪክ መዝገብ ያልሠፈሩ ግን ደግሞ አለም ያወቃቸው ቱባ ባህሎችና ድንቅ ታሪኮች ያላት ኢትዮጵያ በታሪክ … [Read more...] about “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት”
“ውትድርና ሕይወቴ ነው”
ኢትዮጵያዊያን በሀገራችው ሰማይ ስር የመጣን ጠላት በማሽመድመድ ካስመዘገቡት ደማቅ ታሪክ ፊት ለፊት ትልቁን ድርሻ ከሚወስዱት አንዱ ናቸው። ለሀገራቸው በዋሉት ውለታ ከሚተረክላቸው ቀዳሚ ባለ ታሪኮች ቀድመው ይጠቀሳሉ። ሙሉ ህይወታቸውን ለሀገራቸው የሰጡ ናቸው። ጀግና ተዋጊ፣ የበቁ የጦር መሪ፣ የተሳካላቸው የጦር አዛዥ ሆነው አገልግለዋል። በበርካታ የጦር ሜዳ ውጊያዎች ተሳትፈው የሀገርን ሉዓላዊነት፣ የህዝብን ነፃነት ያስከበረ ደማቅ ድል አስመዝግበዋል። ብርጋዲየር ጄኔራል ተስፋዬ ሃብተማርያም። ጄኔራል መኮንኑ በ1934 ዓ.ም በጉራጌ ዞን ከቸሀ ወረዳ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሲሰ መንደር ተወለዱ። የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውንም እዚያው እምድብር ከተማ ተምረው በ1948 ዓመተ ምህረትም አጠናቀዋል። ከ1949-1952 ዓ.ም ድረስ አምቦ የእርሻ ልማት … [Read more...] about “ውትድርና ሕይወቴ ነው”
መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው
አየር ኃይል የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን አስተማማኝና ዘመናዊ አየር ኃይል የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በተለይም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ አየር ኃይሉ በሁሉም ረገድ በመዘመንና ስኬታማ በመሆን ሀገር የምትኮራበት ታላቅ ተቋም መሆኑንም ገልፀዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል አሁን ላይ በውጊያ መሠረተ-ልማት፣ በሰው ኃይል ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራና አጠቃቀም በአጭር ጊዜ ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገቡን በተቋሙ የተለያዩ ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስተማማኝ የሀገር መከታ በመሆን ለየትኛውም ግዳጅ አፈጻጸም ብቁና ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ዘመናዊ ተቋም የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በአየር ኃይል … [Read more...] about መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው