• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የስብሃት ነጋ ወንድም በሌብነት ተያዘ

July 7, 2020 09:47 pm by Editor 3 Comments

አቤሴሎም ነጋ የተባለውና ነዋሪነቱ በአውስትራሊያ የሆነው ስብሃት ነጋ ወንድም 4 ሚሊዮን የአውስትራሊያ ዶላር (2.8 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር) በማጭበርበርና በመስረቅ መከሰሱን Herald Sun ዘገበ።

እኤአ ከ2008 – 2019 ባሉት ዓመታት የ54 ዓመቱ አቤሴሎም ነጋ የተለያዩ የፋይናንስ ወንጀሎችን በመፈጸም ነው 4.2 ሚሊዮን የአውስትራሊያ ዶላር ወደ ግል የባንክ ሒሳቡና iEmpower በሚል ለሚመራው የግል ድርጅቱ ሒሳብ እንዲገባ ያደረገው። ወንጀሉ ስርቆት ብቻ ሳይሆን በኑሯቸው ዝቅተኛ ለሆኑ የሚሰጠውን (የዌልፌር) ገንዘብን አጭበርብሮ መውሰድም የሚጨምር ነው።  

አቤሴሎም ከዘረፈው ገንዘብ ውስጥ $25,300 የሚሆነውን ያጭበረበረው ከሕግ ጋር ችግር ያለባቸውን የአፍሪካ ወጣቶችን ለመርዳት ከተቋቋመ ድርጅት በመስረቅ ነው።

ከዚህ በተጨማሪ አቤሴሎም የቪክቶሪያ ጠቅላይ ግዛት የእኩል ተጠቃሚነትና የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የቦርድ አባል ለመሆን ብሎ ባቀረበው ሰነድ ማጭበርበሩና መዋሸቱ ተደርሶበታል። በዚሁ ጠቅላይ ግዛት ታዋቂ የአፍሪካውያን ማኅበረሰብ ተወካይ ሆኖ ይጠቀስ የነበረውን አቤሴሎም፤ ፖሊስ ለሁለት ዓመታት ሲከታተለው እንደነበር የዜና ዘገባው ያስረዳል። ክሱ እስካሁን ሊዘገይ የቻለው በየጊዜው ሲለዋወጣቸው የነበሩትን የስልክ ንግግሮች ለማስተርጎም ጊዜ በመውሰዱ ነው።

የመርማሪዎቹ መረጃ እንደሚጠቁመው አቤሴሎም የሃሰት ሰነዶችን በማቅረብ iEmpower ለተባለው ድርጅቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠር ጥሬ ገንዘብ “ባፋጣኝ ገንዘብ ያስፈልጋል” በሚል እያምታታ ሲወስድ መኖሩን ያመለክታል። ይህንን ወንጀሉን ለመደበቅ በየዓመቱ በሚያወጣው የፋይናንስ ዘገባ መረጃ በመደበቅ ሪፖርት ያደርግ እንደነበር ተደርሶበታል።

በሌብነት የተከሰሰው አቤሴሎም ወሳኝ ከሆኑ የጠቅላይ ግዛቱና የፌዴራል መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ትሥሥር በመፍጠር ለመታወቅ የበቃ ሲሆን ኅብረባህላዊ ጉዳዮችን በተመለከተ በሚዲያ አስተያየት በመስጠት የሚታወቅም ነበር። ከዚህ በፊትም የቪክቶሪያ ግዛት ኅብረባሕላዊ ኮሚሽነር እንደነበር ለመታወቅ ተችሏል።

አቤሴሎም የሃሰት ማስረጃ በማቅረብ ከጥቅምት 2012 እስከ ነሐሴ 2018 የቪክቶሪያ ጠቅላይ ግዛት የእኩል ተጠቃሚነትና የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የቦርድ አባል በመሆን 21,578 ዶላር በማምታታት ለራሱ ያደረገ ሲሆን ለቃልና ጽሁፍ ተርጓሚዎች ዕውቅና የሚሰጠው ባለሥልጣን የቦርድ አባል እንደነበር የወጣው ዘገባ ይጠቁማል።

አቤሴሎም፣ ዳንኤል ነጋ ከተባለ ጋር በማሤር የ iEmpower የኦፐሬሽን መምሪያ ኃላፊ በሆነው ሪቻርድ ራያን ላይ የከፋ ጉዳት ለማድረስ በሚል ተጨማሪ ክስ ቀርቦበታል።

ይህ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዝርፊ፣ ማጭበርበርና ሌብነት በጠቅላይ ግዛቱ ከፍተኛ የድንጋጤ ንዝረት ፈጥሯል። አቤሴሎም በዋስ የተፈታ ሲሆን ፍርድ ቤት ሴፕቴምበር 23 በድጋሚ ይቀርባል።

ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም ሲገዛ የነበረው ህወሃት የተባለው የበረሃ ወንበዴዎች ቡድን በሥልጣን ለረጅም ዓመታት የቆየው እንደ አቤሴሎም ዓይነቶች በሚደጉሙት እንደሆነ ይህ አንድ ማሳያ ነው። ስብሃት ነጋ የተባለው ቀንደኛ የወንበዴ በረኸኞቹ አባት ከሌሎቹ ወንበዴዎች ጋር በመሆን መቀሌ መሽጎ የወንድሙን ዓይነት “ዕድል” እየተጠባበቀ የሚገኝ ይመስላል።

ይህ ወንጀለኞችን ለፍርድ የማቅረብ ሒደት በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥልና በተለይ በፖለቲካው ዓለም በየዕለቱ የዓመጽ ተግባራትን ከሚሰብኩት አንደ ጸጋዬ አራርሳ ዓይነቱ የአቤሴሎም ዕጣ እንዲደርሳቸው ለማድረግ በርትተን መታገል አለብን በማለት ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ተናግረዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News, Social Tagged With: abeselom nega, sebhat nega

Reader Interactions

Comments

  1. Welelaye ke stockholm says

    July 8, 2020 01:38 pm at 1:38 pm

    Hey!

    Thanks … !

    leba zerafi .. derome yetaweke new .. hagerachenene asebdate .. HODAME !!

    “be enkulalu gezya shebtahte nega bekonetetewe noro … mene lengeru esume yawe new ..! ke ayeha yewelache gider ..,. teram temetalche new … !

    ke kelle wede hager kezaem alem akefe lebawe .. werdete new …

    chenkilatchewn dengayi argo fetrowachew ,, torenete ena lebente yewatalchewale .. ewekte keyete yemta engdi .. yemyakute yehane new .

    Reply
  2. T says

    July 8, 2020 10:55 pm at 10:55 pm

    I think this fraud thing must be hereditary.

    Reply
  3. Tesfa says

    July 20, 2020 02:17 am at 2:17 am

    ትዕይንት – በሃረር የኦሮሞ የጅምላ አሳቢዎች ለራስ መኮነን የቆመውን የመታሰቢያ ሃውልት ወረውታል። አንዳንዶች ወደ ላይ እየወጡ ነው። በዙሪያቸው ቆንጨራ፤ በትርና ሌላም ነገር የያዙ ወጣቶች ከደስታ ብዛት የተነሳ ይፈነጥዛሉ። ራቅ ራቅ ብለው የክልል ፓሊሶችና ሌሎችም የጸጥታ ሃይሎች በዝምታ ያያሉ። ፈረሰኛው ተገፍትረው ሲወድቁ መቧረቅ ተጀመረ እልልታው ቀለጠ። የቄሮ ልጆች ጀግንነታቸው ተመሰከረ። የቆመን በማውደም ቀዳሚ ናቸው። መንገድ በመዝጋት የሚስተካከላቸው የለም። የሰው አንገት ለመቅላት፤ ቤትና ንብረት ለማቃጠል፤ ቤ/ክርስቲያን ለማውደም ለኦሮሚያ ነጻነት ታጥቀው ተነስተዋል። የሚገርመው ይህኑ ቪዲዪ እየቀረጽ ሶሻል ሚዲያ ላይ በመለጠፍ ገንዘብ ለማግኘት መጣራቸው ነው። የእንስሳት ክምችት። ይህ ሁሉ ገመና ግን የመጣው ወያኔ ለራሱ ጥቅም ሲል ባሰመረው የአፓርታይድ የክልል ፓለቲካ ነው። አሁን ራሱን በመቀሌ አስጠልሎ ተንኮልን በርቀት ከትግራይ ተወላጅ ከሆኑ ነጋዴዎች፤ ሹፌሮች፤ ወታደሮች፤ ጋዜጠኞችና ሌሎችም ጋር የአብይን መንግሥት ለማፍረስ ሌት ተቀን የሚሰራው ወያኔ የኦሮሞን ጽንፈኞችን ለራሱ መልሶ ሲጠቀምባቸው ማየትና መስማት ልብን ያማል።
    ወያኔ ከጅምሩ ሌባ ነው። ይህ የእኔ የፈጠራና የስም ማጥፋት ወሬ አይደለም። አብረው የታገሉና ዛሬ በህይወት ያሉ የሚመሰክሩት እውነት ነው። ይህ የሌብነት ተግባራቸው ተላላፊ ነው። የተጠጋቸው ሁሉ ሌባና ደም አፍሳሽ ነው የሚሆነው። እኔ የሃበሻው ነገር ግርም ይለኛል። ከወያኔ ጋር ሆነው ሲገድሉ፤ ሲዘርፉ፤ ሲያዘርፉ የነበሩ በውጭ ሃገር ራሳቸውን በሰረቁትና አስቀድመው ባሸሹት የህዝብ ሃብት ሲንደላቀቁ እየተመለከተ ለሚኖርበት ሃገር ሚዲያና ባለስልጣን መ/ቤት ማሳወቅ ለምን እንደሚከብድ አይገባኝም። አሰፋ ማሩን የገደለው የወያኔ ተኳሽ በለንደን ሲጎራደድ ማየት ኦ ሰላም በስምሽ ስንት ግፍ ተሰራ ያስብላል።
    አሁን እንሆ የአቦይ ስብሃት ወንድም በስርቆት መጠርጠርና መያዙ የሚያስገርም አይሆንም። ህይወታቸው ኑሮአቸው ሁሉ በማታለልና በመቀማት በመግደልና በማፈን ላይ የተመሰረተ የደም ሰዎች ናቸው። እሱ ብቻ አይደለም። መቀሌና አዲስ አበባ ላይ የተንጣለለ ቤት ሰርተው እያከራዪና እየኖሩበት፤ በዘመድና አዝማድ ስም ንግድ ቤቶችና ሆቴሎችን ከፍተው እየተንፈላሰሱ ለትግራይ ህዝብ አሁን በጭልፋ ጥሬ ሰፋሪዎች መሆናቸው የቱን ያህል የጭፍን ፓለቲካ አራማጆች እንደሆኑ ያመላክታል። የኢህአዴግ (የወያኔ) የቁልቁለት ጉዞ ጸሃፊ በማሃከላቸው የነበረውን የፓለቲካ መሸራገድና የልጆች ጫዋታ ያየውን የአምስት አመት ገመና አስነብቦናል። የገባኝ እንዴት በህዝባችን ላይ ሲያላግጡ እንደነበረ ነው። ዛሬም የትግራይን ህዝብ ተከበሃል፤ ታጠቅ፤ ወደ ሃገርህ ተመለስ የሚሉት ፈንጅ ማጥመዳቸውን ስለሚያውቁና እሳትም እየጫሩ ስለሆነ ከሞትን አንድ ላይ እንሙት አይነት ጥሪ ነው እንጂ ለትግራይ ህዝብ አይገዳቸውም። በአዲስ አበባ ከካዝና በብዙ ቶን ቡና ሲዘረፍ አቶ መለስ ያሉት “የሚሰርቁትን እጃቸውን እንቆርጣለን” ነበር። አይ እንዴት ተደርጎ የራስ እጅ በራስ ይቆረጣል። ለፓለቲካ ፍጆታ ግን እንዲያ ነበር የደነፉት። የወያኔ ሌብነት ሃገርና መርከብ እስከ መሸጥ ድረስ ነው።
    ለፍላፊው ጌታቸው ረዳ በቅርቡ ወደ ሃውዜን ብቅ ብሎ ታጠቁ፤ ተዘጋጅ ምሽግ ቆፍሩ ወዘተ ያለው በሃውዜን ላይ የሰሩት ግፍ ተረስቷቸው ይሆን? አይደለም። ግን ለወያኔ የሰው ህይወት የዝምብ ያህል ነው። የሃውዜን ገቢያ በደርግ ያስደበደቡት ራሳቸው አሽልከው ባስገቧቸው ሰዎች የተሳሳተ መረጃ ለደርግ አቀብለው እንደሆነ ታሪክ ይመሰክራል። ጭፍኑ ደርግም ወያኔ ገቢያ ውስጥ ይኖራል በማለት ህዝባችን ጨፈጨፈው! አይ ጊዜ በሰው ህይወት ላይ ትላንትም ዛሬም ቀልድ! ከወደ መቀሌ ወደ ሌሎች የሃገሪቱ አካባቢ የሚሄደው ስሚንቶ የጠፋው ምሽግ እየሰሩበት ይሆን? የአንደኛው ዓለም አይነት የጦርነት ስልት በ 21ኛው ዘመን። ከማን ጋር ይሆን የሚዋጉት? ከኤርትራ፤ ከዶ/ር አብይ አይደለም ከራሳቸው ጋር እንጂ!
    የአቶ ስብሃት ነጋ ወንድም በዝርፊያ መያዙ እግዚኦ አያሰኝም። ሙያው ነውና! የሌብነት ካባን የለበሰ ሰው ምን ጊዜም አጣም ኖረውም መስረቁ አይቀርም። ልምድ ነውና። ጠለቅ ያለ ምርመራ ቢደረግ ምን አልባት ከአቶ ስብሃት ጋር የሚያይዘው ሌሎችም የስርቆት ወንጀሎች ይኖራሉ ባይ ነኝ። ያው ስብሃት ነጋ ደግሞ የወያኔ የነፍስ አባት ስለሆነ ዘረፋው ሃገራዊና ዓለም አቀፋዊ መልክ ይዞ ወያኒያዊ በመሆኑ እልፍ ጉድ ሊወጣ ይችላል። የጉድጓዱ ሚስጢር የሚለው መጽሃፍ ታወሰኝ። ገጣሚው እንዳለው ነው።
    እውነትን ፍለጋ በቆፈርነው ጉድጓድ
    እህል ዘራንበት በልተን እንድናድር።
    እውነት ቢዚህ ምድር ላይ አለች? የት ናት። እነማን ጋ? ለምን ትላንት ያለቀሱ አይኖች ዛሬም ያለቅሳሉ? ለምን መሞት ያለባቸው ቆመው እየሳቁ ረጅም አስበው ሌት ተቀን እየሰሩ ለመኖር የሚታገሉት አፈር ይመለስባቸዋል? አለም አንቺ አለም ምኑ ጋ ቢነኩሽ አቤት ብለሽ ለዚህ ሁሉ ጥያቄ ምላሽ ትሰጭ ይሆን? አላውቅም። ግን ሌባውም ስርቆቱን ይቀጥል። ዘረኛውም የቆመውን ያፍርስ፤ ያቃጥል። ግን የነገር ሁሉ ማክተሚያ አለው። ምን አልባትም እንዲህ ያቅበዘበዛቸው ኮቪድ 19 ዲዲቲ እንደተነፋበት ተባይ ሊያንጠባጥባቸው ይሆናል። ቆይቶ ማየት ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule