• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአባዱላ አጣብቂኝ

December 22, 2017 03:52 pm by Editor Leave a Comment

ከሁለት ወራት በፊት “ … አሁን በደረስኩበት ደረጃ በዚህ ኃላፊነት ለመቀጠል የማያስችሉኝ ሁኔታዎች ስላሉና ፍላጉቱም ስለሌለኝ ለመልቀቅ ድርጅቴንና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን ጠይቄያለሁ” ያለው አባዱላ ገመዳ ዛሬ ኦህዴድን ለህወሓት ሲያግባባ በገሃድ ታይቷል።

“የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በአዲስ አበባ ከተማ ያለውን ህገ-መንግስታዊ ልዩ ጥቅም አስመልክቶ በወጣው ረቂቅ አዋጅ ላይ ህዝባዊ ውይይት ለማካሄድ” በሚል ህወሓት የሚዘውረው “ፓርላማ” ዛሬ ስብሰባ ጠርቶ ነበር። የኦህዴድ ተወካዮች በኦሮሚያ ችግር እያለ፤ የኦሮሞ ሕዝብ በረቂቅ አዋጁ ላይ በአግባቡ ሳይወያይ እንዲሁም የሁሉም አካባቢ ተወካዮች ሳይገኙና በአገሪቱ በአጠቃላይ ያለው ችግር ሳይፈታ ውይይት ማድረግ ተገቢ አይደለም ብለው ተቃውሞ አሰምተዋል።

ከወራት በፊት “አሁን በደረስኩበት ደረጃ በዚህ ኃላፊነት ለመቀጠል የማያስችሉኝ ሁኔታዎች ስላሉና ፍላጉቱም ስለሌለኝ” ከሁሉም ነገር እለቃለሁ ብሎ መግለጫ የሰጠው አባዱላ በዚያው መግለጫው ላይ “ጥያቄዬ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር አፈ ጉባዔነት የመልቀቅ ቢሆንም፣ የመረጠኝን ሕዝብና ያስመረጠኝን ድርጅት ስለማከብር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነቴ እቀጥላለሁ። ከዛ ውጪም ለሕዝብ ይጠቅማል በምላቸው ሥራዎች ባለኝ ጊዜ ተሰማርቼ የማገለግል ይሆናል” ማለቱ የሚታወስ ነው። የዛሬው የማግባባት ተግባሩ ከየትኛው ጎራ እንደሚያሰልፈው ጉልህ ማስረጃ የሰጠ ነው ተብሏል።

በዛሬው የህወሓት ስብሰባ ላይ ከህወሓቱ አስመላሽ ወልደሥላሴ ጋር በመሆን ስብሰባውን የተቃወሙትን ለማግባባት ሲጥር የተስተዋለው አባዱላ “… በክልሉ (በኦሮሚያ) ውስጥ ችግር ቢኖርም ምክር ቤቱ ስራውን መስራት ስለሚጠበቅበትና ጉዳዩም የተለያዩ በመሆኑ ውይይቱ መቀጠል አለበት … እስካሁን የህዝብ ውይይት አለመደረጉ ስህተት ነው፤ በመሆኑም አሁን የባለድርሻ አካላት የተካተቱበት ጭምር በመሆኑ ቢቀጥል የተሻለ ነው፤ ሃሳቦች ማንሳት፣ መከራከርና ማዳበር ተገቢ ሲሆን፤ ቀጣይ የሚነሱ ሃሳቦችን በመያዝ ምክር ቤቱ የሚወስንበት ጉዳይ ይሆናል” በማለት ተናግሯል።

“የለውጥ አራማጆች” ተነስተዋል በሚባልበት እና የእርሱም የሥልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ከዚሁ የለውጥ ማዕበል ጋር የተያያዘ ነው በሚል ሲዘገብለት የነበረው “ጃርሳው” ከኢህአዴግ የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ በኋላ ጀርባውን ለኦህዴድ መስጠቱ ሁሉንም ነገር በዜሮ የሚባዛው ሆኗል።

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ “አባዱላ ወደ ጨፌ ወይስ ወደ ሸቤ” በሚል ባተመው ዘገባ ላይ ይህንን ብሎ ነበር፤ የሰበር ዜና ልክፍት የተጠናወተው የዘመኑ “ሚዲያ” የአባዱላን ከአፈጉባኤነት መልቀቅ በሰበር ዜናነት ማናፈሱ ቆም ብሎ ላየው ራስን ትዝብት ላይ የሚጥል ነው። የአባዱላ መልቀቂያ ማስገባት “ምስጢር” በቅርቡ የሚለይለት ቢሆንም በህወሓት ተለክቶና ተጠፍጥፎ የተሠራ ድርጅትና ስብዕና ያለው ለዚህ ዓይነት የሞራል ልዕልና ይደርሳል ብሎ መገመት ህወሓትን ካለማወቅ ወይም ራስን ከመሳት የሚመነጭ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም።

በበርካታ የሙስና ተግባራትና ህይወት ማጥፋት አለበት እየተባለ የሚነገርለት አባዱላ ከቀድሞው የኢትዮጵያ ሠራዊት ተማርኮ በሻዕቢያ ፈቃድና በህወሓት ፈጣሪነት አዲስ ስብዕና ተሰጥቶት ኦህዴድ የሚባል የጀመረ መሆኑ የሚዘነጋ አይደለም። ይህ ስብዕናው ህወሓት በህንፍሽፍሽ ልትበታተን ስትል የኦሮሞውን ክንፍ ይዞ መለስን የታደገ በመሆኑ ባለውለታነቱ ለማን እንደሆነ በድጋሚ ያስመሰከረ ሆኗል። (ፎቶዎቹ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተወሰዱ ናቸው)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: abadula, eprdf, Ethiopia, Full Width Top, gemeda, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአብን “ፀሐይ” ጎንደር ላይ ጠለቀች April 22, 2021 09:48 pm
  • ተፈትነን እንጂ ወድቀን አናውቅም April 22, 2021 10:55 am
  • ፍፁም ብርሃኔና ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ዋሉ April 16, 2021 10:06 am
  • “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ April 16, 2021 08:45 am
  • “ተዋግተን አይደለም ስንተኛ ብንውል እንኳን መቀሌና አዲስ አበባ አይገቡም” ጄኔራል ባጫ April 14, 2021 09:06 am
  • የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ April 14, 2021 08:53 am
  • “ኤርትራዊ ነን” በማለት የመኖሪያ ፈቃድ ሲቀበሉ የኖሩ የትግራይ ሰዎችን መለየት ተጀመረ April 1, 2021 02:01 am
  • ምርጫ ቦርድ የኦነግን ጥያቄ ውድቅ አደረገ April 1, 2021 01:15 am
  • “እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ April 1, 2021 01:09 am
  • መንግሥት ካልደረሰልን አሁንም ግድያ ይኖራል – ነዋሪዎች April 1, 2021 01:04 am
  • በትግራይ ሊዘረፍ የነበረ የእርዳታ እህል ተያዘ April 1, 2021 12:39 am
  • “በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አልደራደርም” March 24, 2021 01:22 am
  • “ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ March 23, 2021 11:28 pm
  • እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ March 23, 2021 10:23 pm
  • በርግጥ ኢትዮጵያ ዝናብ አዝንባለች? March 23, 2021 10:15 pm
  • አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች March 21, 2021 08:57 pm
  • ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ March 19, 2021 04:32 pm
  • ባልደራስና የአብን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ March 18, 2021 01:56 pm
  • ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም” March 17, 2021 09:54 pm
  • በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ነው – የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት March 17, 2021 04:54 am
  • ምርጫ ቦርድ ከፈቀደለት ኦነግ በምርጫው እንደሚወዳደር አስታወቀ March 17, 2021 04:30 am
  • በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው March 15, 2021 11:25 am
  • በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ March 15, 2021 10:13 am
  • የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ March 15, 2021 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule