ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ የአስፈጻሚውን አካል የሥራ ክንውን በተመለከተ ያቀረቡት ሪፖርትና ለጥያቄዎች የሰጡት ምላሽ። ሙሉውን ለመመልከት የቪዲዮው ምስል ላይ ይጫኑ። … [Read more...] about “የጥላቻና የምቀኝነት አስተሳሰብ መገረዝ አለበት፤ አደገኛ በሽታ ነው”
Archives for June 2018
ከመቀሌው ዱለታ በስተጀርባ ያሉ እውነታዎች
የህወሃት መግለጫ በመስመሮች መካከል ሲነበብ በተቀማ ጩኸት ሊመሰል ይችላል። ከመቀሌው ዱለታ በስተጀርባ የነበሩ እውነታዎችን ለመዳሰስ የፖለቲካ ሊቅ መሆንን አይጠይቅም።ህወሃቶች አብረው ወስነው ያስተላለፉትን ጉዳይ እንደመጋዣ አኝከው ሲያበቁ፤ ከብዙ ገጽ የክስ ቻርጅ ጋር ብቅ ብለዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩን ለማስጠቆር የሄዱበት ርቀት ግልጽ እና መሳጭ ነው። ሰማይ ወጥተው ቁልቁል ቢወርዱም ግን ከቶውንም የህዝብ ቀልብ ሊስቡ አይችሉም። እኛ ከሌለን ሃገር ትጠፋለች ይሉት የነበረው ቁንጽል እሳቤ፤ እነሆ ፉርሽ ሲሆንባቸው፤ አዲስ ካርታ መዘዙ። የአዲሱ ትውልድ መሪዎች፤ ሕዝብን በሃይል ሳይሆን በፍቅር መምራት እንደሚቻል ሲያሳዩዋቸው፣ ወደ ኦሪት ዞር ብለው ከዘፍጥረት መጀመራቸው ይሆን? በአዲሱ ዜማቸው፤ ኢትዮጵያን ትተው ስለ ትግራይ መጮህ የያዙ ይመስላል። "ለነባር አመራሮቻችን እውቅና ይሰጥ" … [Read more...] about ከመቀሌው ዱለታ በስተጀርባ ያሉ እውነታዎች
“ጄኔራል” አደም መሐመድ፤ ከሬዲዮ ኦፕሬተርነት እስከ መረጃና ደኅንነት ዳይሬክተርነት
ወሎ-አምባሰል የተወለደው አደም መሐመድ በ1975 ዓ.ም ኢህዴንን የተቀላቀለ ነባር ታጋይ ነው። በትጥቅ ትግሉ ወቅት በዋናነት የአዲሱ ለገሰ ሬዲዮ ኦፕሬተር ሆኖ ሰርቷል። አንዳንዶች በሰውየው ላይ ሲቀልዱ “የአዲሱ ለገሰ ሻሂ አፍይ” ይሉት ነበር። አደም መሐመድ ለአዲሱ ለገሰ ለአምልኮ የቀረበ ፍቅር ያለው በመሆኑ በሬዲዮ የሚተላለፉ መልዕክቶችን በጽሁፍ ከመገልበጥና መረጃዎችን ከማድረስ ባሻገር ለሰውየው ማሸርገድ ይወድ ነበር የሚሉት የእርሱ ዘመን ጓዶች፣ አድርባይነቱን ያለ ልዩነት ይስማሙበታል። ከኢህአዴግ ምስረታ በኋላ በነበሩ አውደ ውጊያዎች በ“ዘመቻ ዋለልኝ” እና “ኢህአዴግ ፋና” በተሰኙ ዘመቻዎች ላይ ተሳትፏል። በትጥቅ ትግሉ ወቅት እንደ ድርጅት “መስመር ማጥራት” በሚል በተለያዩ ጊዜያት በተካሄዱ ሴሚናሮች፣ ኮንፍረንሶች እና በሁለቱም ድርጅታዊ ጉባዔዎች (1976 እና 1981ዓ.ም) … [Read more...] about “ጄኔራል” አደም መሐመድ፤ ከሬዲዮ ኦፕሬተርነት እስከ መረጃና ደኅንነት ዳይሬክተርነት
“አባ ነቅንቅ” – ኦባንግ ሜቶ ሊሞሸር ነው!!
ከኢትዮጵያውያን ጋር ሁሉ የማይሰበር የጽናት ጋብቻ እንደመሠረተ ያምናል። ከሞት ወዲያ ሳይሆን ለሞት ወዲህ ስላለው ታላቅ አገራዊ ክብር ይጨነቃል። በሁሉም ስፍራ፣ በየትኛውም አጋጣሚ ለሚፈልጉት ሁሉ “አለሁ” የሚል ኢትዮጵያዊ ነው። ዘረኝነትን፥ ዘውገኝነትን፥ ጎሠኝነትን፥ አጥብቆ ይዋጋል፤ ይጸየፋል። ከዘር ቆጠራና ከቂም የጸዳች ኢትዮጵያን ማየት ህልሙ ነው። የመጨረሻው ግብ!! ፍቅርን የሚሰብክ በመሆኑ አፍቃሪዎቹ ከልብ ይወዱታል። ለእሱ ያላቸው ፍቅርም ሲሞቅ በማንኪያ የሚሉት ዓይነት አይደለም። በቅርቡ የመኪና አደጋ ባጋጠመው ወቅት ለአደጋ የዳረገችውን ሴት ከሞት ተርፎ ሲያጽናናት የተመለከተች እናት እንባ እያነቃት አድናቆቷን ችራዋለች። ኦባንግ ሜቶ!! ዛሬ በሁለት አዳዲስ የህይወት ጅማሮ ላይ ነው። “ማኅተቤ” የሚላት አገሩ ተስፋ ሰጪ በሆነ ሽግግር ላይ ናት ብሎ ያምናል። በዚህም … [Read more...] about “አባ ነቅንቅ” – ኦባንግ ሜቶ ሊሞሸር ነው!!
ህወሓት እነ ዓቢይን ለመገምገም ኢህወዴግን ስብሰባ ጠራች
ላለፉት ሁለት ቀናት መቀሌ መሽጋ ስትንጫጫ የቆየችው ህወሓት እነ ዓቢይ አህመድን ለመገምገም ስብሰባ ይጠራልኝ ብላ መግለጫ አውጥታለች። የዛሬውን አያድርገውና ዱሮ በፈለገችው ጊዜና ሰዓት ስብሰባ ስትጠራ የኖረችው ህወሓት ለዚህ መብቃቷ ክስረቷን ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል። ህወሓት ይህንን ስትጠይቅ የሚከተሉትን መሠረታዊ ውሳኔዎች በመቀበል ነው፤ ኢትዮጵያ ህዝብታት ወያናይ ዴሞክራሲ ግንባር (ኢህወዴግ) ወይም በአማርኛ ኢህአዴግ፤ "የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል ለመሸጥ ያስተላለፋቸውን ውሳኔዎች" እንደምትቀበል፤ "የኢትዮ ኤርትራን የድንበር ኮሚሽን ውሳኔና የአልጄርሱ ውይይት በሚመለከት የተላለፈውም ውሳኔ ከአገሪቱ የሰላም ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ በመሆኑ ተገቢና ወቅታዊ ነው" ካለች በኋላ ነው ህወሓት እነ ዓቢይ ይገምገሙልኝ ስትልት ስብሰባ … [Read more...] about ህወሓት እነ ዓቢይን ለመገምገም ኢህወዴግን ስብሰባ ጠራች
ሁለቱ ጄኔራሎች
ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ እና ሜ/ጀኔራል አለምሸት ደግፌ ከመከላከያ ሰራዊቱ በተለያየ ጊዜ “የመከላከያ ሪፎርም አደናቃፊ” በሚል ማዕረጋቸው ተገፍፎ የተሰናበቱ ወታደራዊ መኮንኖች ናቸው። ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ የቀድሞ የጦር ሠራዊት አባል የነበረና በ1978 ዓ.ም ኢህዴንን የተቀላቀለ ጀግና አዋጊ እንደሆነ የኢህዴን ጓዶቹ ሳይቀር ይመሰክሩለታል። ድህረ-ደርግ በሲቪል አስተዳዳሪነት የላስታ ወረዳ አስተዳደር ቀጥሎም የሰሜን ወሎ ዞን አመራር ሆኖ ሰርቷል። የባድመ ጦርነት መቀስቀስን ተከትሎ ወደ ወታደራዊ አመራርነት የተመለሰው አሳምነው ጽጌ፣ የቀደመ የትግል ልምዱን መነሻ በማድረግ ያለአንዳች ማዕረግ በጦርነቱ ውስጥ በባድመ የጦር ግንባር 22ኛ ክፍለ ጦርን እየመራ ተዋግቷል። ባድመ ላይ የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ ሲውለበለብ ከነበሩት ጥቂት አመራሮች አንዱ አሳምነው ጽጌ ይገኝበት … [Read more...] about ሁለቱ ጄኔራሎች
የሱሪ ረዥሙ “ፕሮፌሰር ጄኔራል” ሳሞራ የኑስ ስንብትና የሳዕረ መኮንን መንገሥ
ግንቦት 30/2010 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ ማምሻውን ከወደ ታችኛው ቤተ-መንግሥት የተሰማው ዜና የኢትዮጵያዊያንና የዓለምአቀፉን ሚዲያ ትኩረት የሳበ ነበር። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ (መከላከያ በአዲሱ አወቃቀር በኮሚቴ (ወታደራዊ ካዉንስል) ሊመራ ነው) በሚል ርዕስ ከሦስት ሳምንት በፊት መከላከያ ሠራዊት እንደተቋም በአመራሩ ላይ ብወዛ ሊያደርግ መሆኑን የሚገልጽ መረጃ ወደአንባቢያን አድርሶ ነበር። በወቅቱ ወደ አንባቢያን ባደረስነው መረጃ ላይ፡- መከላከያ ሠራዊት ሪፎርም ሊያደርግ እንደሆነ፣ በአገሪቱ “ሕገ-መንግሥት” ላይ የሌለ ቢሆንም ሦስት ምክትል ኤታማዦሮች መሾማቸውን፣ የ“ኤታማዦር ኮሚቴ” በሚል የቡድን አመራር መከላከያ ሠራዊት ሊመራ እንደሆነ፣ የመከላከያ ሠራዊት “ወታደራዊ ካውንስል” እንደ አዲስ ሊደራጅ እንደሆነ፣ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ … [Read more...] about የሱሪ ረዥሙ “ፕሮፌሰር ጄኔራል” ሳሞራ የኑስ ስንብትና የሳዕረ መኮንን መንገሥ
የታሪክ ፈተናችን እና ያሬዳዊ ትዝታ፤ ከክላሽ እስከ ብዕር!
የለውጥ ውርጃ፣ የዘመናዊነት መጨናገፍ፣ የህዝባዊ ኃይል (ድምጽ) ተጽኖ ፈጣሪነት መኮላሸት፣…ድግግሞሻዊ የታሪክ አዙሪት አምሳያ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ በተከታታይ ትውልዶች የደም ጎርፍ እየተንሳፈፈች እዚህ ደርሳለች። የአገር ግንባታ ሲሚንቶ ውሉ አልይዝ ብሎ ንቃቃት በዝቶበት የታሪክ ፈተናዋን መሻገር የተሳናት ኢትዮጵያ፤ በውስጣዊ ቅራኔ እንደተናጠች፣ ቅራኔዎቹ በተከታታይ ትውልዶች የደም ጎርፍ ከቶም እየተባባሱ የማህበራዊ ትስስሮሽ ነባር ህሊናዎች እየተናጉ፣ ዘውጋዊ መስመሮች በስታሊናዊ “ዕይታ” የልዩነት መስመሮች እየጎሉ፣ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶች እየሻከሩ፣ ደም መቃባቱ እየበዛ በመሄዱ አገሪቱ ወደመፍረስ ጠርዝ በመገፋት ሂደት ላይ ትገኛለች። ከየትኛውም ጊዜ በከፋ መልኩ የርስ በርስ መጠራጠርና አለመተማመን ከፖለቲካ አደባባዩ ተሻግሮ በየግለሰቡ ጓዳ ገብቷል። በደብተራ ፖለቲካ ስትታመስ … [Read more...] about የታሪክ ፈተናችን እና ያሬዳዊ ትዝታ፤ ከክላሽ እስከ ብዕር!
በማንነት ማፈናቀልን እንዴት መቀነስ ይቻላል?
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ‘የማንነት’ እና ‘የብሔር’ ፖለቲካ ወይም ጥያቄ ተምታተዋል። ብዙ ግዜ ሁሉም ነገር ‘የብሔር ጥያቄ’ ነው፤ መልሱም የሚገኘው ‘በብሔርተኝነት’ ነው የሚባለው ጉዳይ ከማንነት ጋር የተያያዘውን ጥያቄ ያድበሰብሰዋል። እንዲያውም አንዳንዴ ብሔርተኝነት ችግሩን ሊያባብሰው ይችላል። የማንነት ወይም የብሔር ትርጉሙም እንዲሁ የተምታታ ነው። ምክንያቱም ማንነትም ይሁን ብሔር በተለምዶ የሚበየነው በቋንቋ ላይ ተመሥርቶ ነው። ስለዚህም በተምታታ ትርጉም ላይ የተመሠረተ ብሔርተኝነትም ለተሳሳተ ጥያቄ የተሳሳተ መልስ ለመስጠት ይዳርጋል። ማንነት በቋንቋ ሊመሠረት ይችላል፤ ነገር ግን አንድ ቋንቋ እየተናገሩ የተለያየ ማንነት ያላቸው ግለሰቦች ወይም ሕዝቦች አሉ። ማንነት በፆታ ብቻ ሊወሰን ይችላል። ወይም ደግሞ በፆታዊ ግንኙነት ምርጫ ሊወሰን ይችላል። በመልክ ወይም በቆዳ ቀለም። … [Read more...] about በማንነት ማፈናቀልን እንዴት መቀነስ ይቻላል?
The First Peaceful Coup d’état Led by Team Lemma
In September 2016, my article entitled “A glimpse into the plausible alternative futures of Ethiopia”was posted on some Ethiopian websites. By employing one of the tools I use as I facilitate strategic planning sessions- Scenario Planning, I showed the four alternative futures of Ethiopia (see the attached pic) and pleaded both the ruling party and oppositions to sit down and negotiate to avoid bloodshed and chaos. When I wrote this futuristic commentary, both sides were seemingly strong with … [Read more...] about The First Peaceful Coup d’état Led by Team Lemma