በህወሃት/ኢህአዴግ ከፍተኛ የገንዘብ ድጎማና ድጋፍ ለዓለም የጤና ጥበቃ ድርጅት ዳይሬክተርነት የሚወዳደረው ቴድሮስ አድሃኖም የመመረጡ ጉዳይ አደጋ ገጥሞታል፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በነበረበት ወቅት ሦስት የኮሌራ ወረርሽኞች በምሥጢር እንዲያዙ ማድረጉ ለዳይሬክተርነት እንዳይበቃ ያደርገዋል ተብሏል፡፡ እንደ አሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ይህ ጉዳይ የቴድሮስ “የጥቅምት ዱብ ዕዳ” ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡ ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ ሜይ 13፤2017 ዓም “የዓለም ጤና ጥበቃ ድርጅትን ለመምራት የሚወዳደረው እጩ ወረርሽኝ በመደበቅ ተከሰሰ” በሚል ርዕስ ባስነበበው ዜና የቴድሮስን የመመረጥ ተስፋ ስለሚያጨልመው የኮሌራ ወረርሽኝ ምሥጢር በዝርዝር አትቷል፡፡ በያዝነው የግንቦት ወር (ከሜይ 22፣ 2017) ጀምሮ በጄኔቫ በሚካሄደው የአንድ ሳምንት ስብሰባ ድርጅቱን ለመምራት ከሚወዳደሩት ሦስት … [Read more...] about የኮሌራው ምሥጢር! የቴድሮስ “የጥቅምት ዱብ ዕዳ”?
Archives for May 2017
ፍትህን ሰቀለው በፍትህ ስም የፕሮፓጋንዳ ዳንኪራ – የጨለማው ሳምንት!!
የ“ፍትህ” ወይስ የጨለማ ሳምንት? (ርዕሰ አንቀጽ) “ገንዘብ ሲናገር ፍትህ ጸጥ ይላል!” ይህ የተጻፈው በአንድ የጎንደር እስር ቤት ውስጥ ነው። የተጻፈው በግድግዳ ላይ ሲሆን በብዕር ወይም በቀለም አይደለም። ፍትህ ከተጓደለባቸው አንዱ የእጁን ጣት በመብጣጥ በደሙ ነው። ፍትህ የተዛባባቸው ይህንኑ አባባል ልክ እስር ቤት እንደገቡ ይሳለሙታል። በብዙ የአገሪቱ ማጎሪያዎች ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት ገላጭ ሃረጎች ይጻፋሉ። ፍትህን አደባባይ ሰቅለው በምስኪኖች ህይወት ለሚጫወቱ ይህ ሁሉ ስላቅ ነው። ፍትህን አደባባይ ሰቅለዋት፣ በፍትህ ስም እየማሉ በድግስ ሊያሽካኩ ይወዳሉ። ፍትህ የዜጎች ሁለንተናዊ ህይወታቸው ትርጉም የሚያገኝበት ውድ ጉዳይ ነው። ይህንን ሃቅ የበረሃው አባዜው አልለቅ ያለው ህወሃት ጥንቅቆ ያውቀዋል። ሊክደውም አይችልም። ለዚህም ነው “ህገ መንግስት፣ ህግ፣ አዋጅ፣ የሰብዓዊ … [Read more...] about ፍትህን ሰቀለው በፍትህ ስም የፕሮፓጋንዳ ዳንኪራ – የጨለማው ሳምንት!!
ገድለህ ማረው
የሰራህን በዓይንህ አይተህ ሲወሻክት ወይም ሰምተህ ልታቆመው ብትነሳ በዝምታ ፊት ብትነሳ አፍሮ ይተው እንዳይመስልህ ስምህን ነው ሚከትፍልህ ከዛ - ይልቅ ነገርህን አ’ርገህ ድብቅ ትንሽ ጊዜ ብትጠብቅ እንደወትሮው ሱሱን ሊያደርስ ካ’ንዱሊቀምስ ካ’ንዱ ሊልስ ከሰው ጋራ ሲቀላቀል ባልታሰበ የፊት ተንኮል ተይዞልህ ፊትህ ሲቀል መፋረጃህ ያን ጊዜ ነው ተቀላቅለህ አብረህ በለው ወይንም በዓይንህ ገድለህ ማረው (ወለላዬ ከስዊድን) … [Read more...] about ገድለህ ማረው
ተቦርነ በየነ “አንተ አልክ?” – ቴዲ አፍሮን
እንዲህም ሆነ። የይሁዳ ገዥ የነበረው ጲላጦስ ክርስቶስን አስጠርቶ "አንተ የአይሁድ ንጉስ ነህን?" ሲል ጠየቀው። ክርስቶስም መልሶ "አንተ አልክ?" አለው። ሰማይን ያለ ምሰሶ ያቆመው ክርስቶስ "ጥፋ" የምትል ቃል ብቻ ከአንደበቱ ቢያወጣ ኖሮ ጲላጦስ አይደለም መላው ቂሳር ክምድረ-ገጽ በጠፉ ነበር። ታዋቂዎች በአዋቂዎች ላይ የሚቀልዱበት ይህ የገሃዱ አለም እውነታ ግብረ-ገብ ወደ ግብግብ በተቀየረበት በዚህ ዘመን ባሰበት እንጂ አልጠፋም። ጥንት አንቺ-ትብሽ፣ አንተ-ትብስ ይባል የነበረው ብሂል አሁን በ“አንቺ ብስብስ አንተ ብስብስ” ተቀይሯል ሲል አንዱ አጫወተኝ። ከቶውንም ስድብን እንደ ስንቅ በከረጢት ቋጥረው በሚጓዙበት የፌስቡክ ዘመን መስመር የመልቀቁ ነገር አዲስ ሊሆን አይችልም። "አንተ አልክ?" ብሎ ማለፍ ምን ይጎዳል? ብላቴናው ላይ አንዳች እንከን ሲያጡ፣ የጠወለገን የጥላቻ … [Read more...] about ተቦርነ በየነ “አንተ አልክ?” – ቴዲ አፍሮን
እንባ ካለ አሁን እናልቅስ!! ሊታመን ባይችልም አማኑኤል ሆስፒታል እንዲህ እየሆነ ነው!
“ቅባትና ደረቅ” በአማኑኤል የአዕምሮ ህክምና ሆስፒታል ታካሚዎች እንደ ደረጃ መዳቢ የተሰጠ ስም ነው። ታሪኩ ዘግናኝ፣ ኅሊናን የሚፈትን፣ ወዴት እያመራን እንደሆነ ግራ የሚያጋባ፣ መፈጠርን የሚያስጠላ፣ ሲሰሙት ግራ የሆነ፣ ቃላት ሊገልጹት የማይችል የክሽፈታችን ሁሉ ከሽፈት ነው። አማኑኤል ሆስፒታል ተኝቶ ለመታከም አርባ ሺህ ብር እንደሚከፈል ከመስማት በላይ ዘግናኝ ጉዳይ የለም። ጎልጉል ባሰባሰበው መረጃ ሌሎችም ጉዳዮች አሉ። በአማኑኤል ሆስፒታል ሴት የአዕምሮ ህመምተኞች መደፈራቸውን፣ ሲያረግዙ ጽንስ የሚቋረጥበት ክሊኒክ በውስጥ በተደረገ ስምምነት ይሰጥ እንደነበር ይፋ በተሰማ ጊዜ ጫጫታ ተሰምቶ ነበር። ጉዳዩን በወቅቱ ይፋ ያደረጉት አንድ የሆስፒታሉ ነርስ ነበሩ። ዛሬ ያ ግፍ ተመርምሮ መልስ ሳያገኝ ተጨማሪ ጉድ እየሰማን ነው። የሟቹ መለስ ዜናዊ ባለቤት የበላይ ጠባቂ ሆና ስትመራው … [Read more...] about እንባ ካለ አሁን እናልቅስ!! ሊታመን ባይችልም አማኑኤል ሆስፒታል እንዲህ እየሆነ ነው!
“ደሸት” የብርሃን እውነት!
“ደሸት” የብርሃን እውነት! የማጂ፣ የጂማ፣ የመንዲ፣ የመደባይ አባት የማራ፣ የዥማ፣ የገንቲ፣ የአሬቲ ... አያት የአማራው፣ የኦሮሞው፣ ... የዘር ግንድ አውራ የመተሳሰሪያ እውነተኛ ምንጭ አሻራ! “ደሸት” ኢፋ ዹጋ ፍጥረተ ማለዳ የዘር ሀረግ ገመድ ምስጢራዊ ጓዳ አባ ቃሉ አባ ውሉ አያ ፍቅሩ ትስስሩ ዘረ ሸጋ ኢፋ ዹጋ መሆንህን አምኖ አማራ ኦሮሞ ስምህን በስሙ አትሞ “ደ”ን ደግ ብሎ አንብቦ “ሸ”ን ሸበበ ብሎት አንግቦ “ት”ን ትስስር ይለዋል ውልደቱን ከትቦ “ደሸት” የዘር ምንጩ አባ እቅጩ ስመ ክብሩ ውስጠ ምስጢሩ “ደሸት” የብርሃን እውነት! (ኢፋ ዹጋ!) ዘሩን ሲያበዛ ሲዘረጋ ማጂ፣ ጂማ፣ መንዲ፣ መደባይ ብሎ ሰይሞ የዘር ሲሳይ መደባይ ስሙን ከስሙ … [Read more...] about “ደሸት” የብርሃን እውነት!
የኢትዮጵያ አርበኞች ውለታና የባንዳዎች ዕዳ!
ረዥሙ የኢትዮጵያ ታሪክ ከነፍጥ፤ ከሞፈርና ከመስቀል ጋር ተዛማጅነቱ ፍፁም ነው ማለት ይቻላል፡፡ ለዚህ ይመስላል አባ ዳኘው (ዳግማዊ አጤ ምኒልክ) የአድዋ ጦርነት ዘመቻ ዝግጅት ላይ “… ሀገር የሚያጠፋ፤ ሃይማኖት የሚለዉጥ ጠላት…” መጥቷልና ከርስትህና ከሚስትህ ሳትነቀል የሚል ይዘት ያለው አዋጅ በወቅቱ እንዲነገር ያደረጉት፡፡ በጊዜ ሂደት ሀገሪቱ ከታሪኳ መድረክ “መስቀል”ን ገለል ብታደርግም ነፍጥና ሞፈር (ርስት) የአገሪቱ ህያው አምሳያ የታሪክ አካል ሆነዉ ቀጥለዋል፡፡ ወራሪ ኃይል በመጣ ቁጥርም እነዚህ የአገሬው ማታገያ አብይ አጀንዳዎች ሆነው ሲነሱ ኖረዋል፡፡ የነጮቹ ቅርጫ የሆነችው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ክፉ ዕጣ ውልቅልቋ ሲወጣ፤ ኢትዮጵያ አድዋ ላይ በጀግኖች አባቶቻችን ተጋድሎ ሉአላዊነቷን ማስከበር ችላ ነበር፡፡ ፋሺስት ጣሊያንም ሽንፈቷን በእልህና በቁጭት ለመቀበል አርባ … [Read more...] about የኢትዮጵያ አርበኞች ውለታና የባንዳዎች ዕዳ!
ህወሓት: በነፃ ፕሬስ መቃብር ላይ የቆመ አገዛዝ!
ኢትዮጵያ በፕሬስ ነፃነት ከዓለም 150ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች! አገሪቱ የነፃ-ሚዲያ ባለቤት የምትሆነው በህወሓት መቃብር ላይ ነው! ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እና ድጋፍንም ሆነ ተቃውሞን ምክንያታዊ በሆኑ ነገሮች መግለጽ የሚችልና ፖለቲካዊ ንቃት ያለው ማህበረሰብ ለመፍጠር የሚደረገው ትግል፤ ካለ ነፃ ፕሬስ ተዋፅኦ ስሙር ሊሆን የሚችል አይደለም፡፡ ገዥው ኃይል የግሉ ፕሬስ ለአገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና አሳታፊነት ያለው የፖለቲካ ሥርዓት እንዲፈጠር የራሱን በጎ ሚና እና አበርክቶ እንዲወጣ ምቹ የሥራ ምህዳር ከመፍጠር ይልቅ በትዕግስት አልባ ባህሪው የተነሳ በነፃ ፕሬሱ ላይ የተለየ ሃሳብና የፖለቲካ አመለካከት በተንፀባረቀ ቁጥር በመደንበር ሚዲያዎቹን በመዝጋት፣ በግልፅ የተደነገገውን ህግ በህብዑም ሆነ በግላጭ ሲንደው ታይቷል፡፡ በውጤቱም፤ በየዓመቱ የዓለም … [Read more...] about ህወሓት: በነፃ ፕሬስ መቃብር ላይ የቆመ አገዛዝ!
የነፃነት ኃይሎች ጥቃት ከዳር ወደ መሀል!
ጎንደርና ባህርዳር ከተማ ውስጥ በሁለት ወር ብቻ 9 የቦምብ ፍንዳታ ደርሷል! “ህወሃት የሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያን ክፍል የበቀል መወጫ እያደረገው ነው”፤ ነዋሪዎች ላይቆም የተቀጣጠለው የሰሜን ምዕራብ ብረት አከል ህዝባዊ አመፅ የትግል ስልቱን እየቀያየረ ባህርዳር ደርሷል፡፡ አስር ወራትን ያስቆጠረው የነፃነት ኃይሎች እንቅስቃሴ ከገጠር ሽምቅ ውጊያ ወደ ከተማ የደፈጣ ቦምብ ጥቃት ተሻግሯል፡፡ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ዘጠኝ የቦምብ ፍንዳታ ደርሷል፡፡ ድርጊቱ ሰላም የነሳው ህወሃት “የአማራ ክልልን የበቀል መወጫ እያደረገው” መሆኑ ይነገራል፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ ሙሉ የደህንነት አቅሙንና የበዛ የመከላከያ ኃይሉን አማራ ክልል ላይ ቢያደርግም የነፃነት ኃይሎች ተከታታይነት ያለው ጥቃት ከመፈፀም ያገዳቸው ኃይል የሌለ መሆኑ እየታየ ነው፡፡ የመጀመሪያዉ ዙር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ … [Read more...] about የነፃነት ኃይሎች ጥቃት ከዳር ወደ መሀል!