Your Excellency, To Permanent Representatives of Members and Observer States of the UN Human Rights Council Geneva, 25 May 2017 RE: Addressing the pervasive human rights crisis in Ethiopia Your Excellency, The undersigned civil society organisations write to draw your attention to persistent and grave violations of human rights in Ethiopia and the pressing need to support the establishment of an independent, impartial and international investigation into atrocities committed by security … [Read more...] about HRC35: Addressing the pervasive human rights crisis in Ethiopia
Archives for May 2017
ፍልሰት፤ ልመናና የጎዳና ህይወት በአዲስ አበባ!
“በመንገዶች አምራ በፎቆች ተውባ” የህወሃት/ኢህአዴግ ኩራት የሆነችው አዲስ አበባ “አገሪቱ አሁን ያለችበት ሂደት በእሳት ላይ ተጥዶ እንደሚንተከተክ ማሰሮ ትመስላለች” አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ሁሉ ነገር ነች፡፡ ከተማዋ ከፖለቲካ ከተማነቷ ባሻገር የኢኮኖሚና የማህበራዊ ዘርፎች ማዕከል መሆኗ የብዙዎችን ትኩረት እንድትስብ አድርጓታል፡፡ በክልሎች የሚታየው የሥራ ዕድል ዕጦት፣ ይህን ተከትሎ የተፈጠረው ሥር የሰደደ ድህነት አዲስ አበባን የከተማ ስደት መከማቻ ማዕከል አድርጓታል፡፡ በርግጥ የከተማ ስደት ስረ-መነሻ ከቀደሙት ጊዜያቶች ጀምሮ የተለያየ መንስኤ አለው፡፡ የኢትዮጵያን የከተማ ስደት ከአገሪቱ ማህበረ-ኢኮኖሚና የፖለቲካ መዋቅር ጋር አስተሳስረው የሚያጠኑ ምሁራን የከተማ ስደትን ከኢትዮጵያ ከተሞች አመሠራረት ጋር አያይዘው የጥናት ውጤታቸውን ያቀርባሉ፡፡ በጥንቱ … [Read more...] about ፍልሰት፤ ልመናና የጎዳና ህይወት በአዲስ አበባ!
ኢትዮጵያ፤ ህወሓትና የትግራይ ወጣት
ኢትዮጵያ ወጣትነትን15-29 ዓመት ባለ የዕድሜ ክልል ከፍላ ትበይነዋለች፡፡ አገሪቱ ውስጥ ካለው የህዝብ ብዛት በአማካይ 60% የሚሆው ወጣት ተብሎ ሊጠቀስ በሚችለው የዕድሜ ክልል ይገኛል፡፡ የተሻለ የትምህርት ጥራት፣ አማራጭ የሥራ ዕድል፣ ምቹ ማህበራዊ አገልግሎት፣ የፖለቲካ ነፃነትና መሰል ወሳኝ ጉዳዮችን አጥብቀው የሚሹት የኢትዮጵያ ወጣቶች ከህወሓት/ኢህአዴግ አፓርታይዳዊ ዘረኛ የፖለቲካ አሰላለፍ ጋር በተደጋጋሚ ሲላተሙ ይስተዋላል፡፡ ለህወሓት/ኢህአዴግ አንድ አይነት ወይንም ተመሳሳይ አጀንዳ የሚያነሳ፣ በዘውጋዊ (በዘረኛ) ማንነት የማይከፋፈል፣ ለአገዛዙ የማያጎበድድ ወጣት “የሥርዓቱ አደጋ” ነው፡፡ በ1997 ታሪካዊ የምርጫ ዘመን የአገዛዙን ዘረኛ የአፓርታይድ አሰላለፍ የማይቀበሉ፣ ከአካባቢያዊ ማንነት ይልቅ የጋራ ማንነትን ያቀነቀኑ ወጣቶችን ከመንግስታዊ ፍጅቱ ጎን ለጎን “አደገኛ … [Read more...] about ኢትዮጵያ፤ ህወሓትና የትግራይ ወጣት
በግብረሰዶማዊያን የተወረረችው አዲስ አበባ!
ግብረ-ሰዶማዊነትን እንደገቢ ምንጭ የሚጠቀሙበት ወንድ አዳሪዎችና (male prostitutes) ደላሎች አሉ! ግብረሰዶማዊያኑ የራሳቸው መገናኛ ቤቶችና ምሽት ክለቦች አሏቸው “ዜጋ” የሚለው ቃል የመግባቢያ ኮድ ሥማቸው ነው! ግብረሰዶማዊያኑ በድብቅ መኖሪያ ቤቶችና በምሽት ክለቦቻቸው “የጋብቻ ሥነሥርዓታቸውን” ይፈጽማሉ! ዳዊት ተሰማ (የባለ ታሪኩ ስም የተቀየረ) በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በድህረ ምረቃ መርሐ-ግብር የህብረተሰብ ጥናት ተመራቂ ተማሪ ነው፡፡ ተማሪው ለዲግሪ ማሟያ ጥናት ለማዘጋጀት ለአማካሪው ካቀረበው የጥናት ሀሳብ አንዱ ግብረሰዶማዊነት በአዲስ አበባ በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ፤ በተለይም ሁኔታውን ከውጪው ዓለም ተጽዕኖ አኳያ በማያያዝ ለማቅረብ ነበር፡፡ የተማሪው የጥናት ሀሳብ በአማካሪው መምህሩ ውድቅ የተደረገ በመሆኑ ሌላ ርዕስ የጥናት ሀሳብ ለመምረጥ … [Read more...] about በግብረሰዶማዊያን የተወረረችው አዲስ አበባ!
ይድረስ ለጀርመን ድምጽ ሬዲዮ የአማርኛ አገልግሎት
ከሸዋ ሕዝብ ድርጅት (Shoa People Organisation (SPO) የተሰጠውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ … [Read more...] about ይድረስ ለጀርመን ድምጽ ሬዲዮ የአማርኛ አገልግሎት
ተስፋዬ ገ/አብ “የሚዲያ ያለህ” እያለ ነው!
ለተስፋዬ ዕድል መስጠት ሬዲዮ RTLM መሆን ነው የኢትዮጵያ ስም ሲጠራ፣ ከፍ ከፍ ሲል “የዘር ወባው” የሚነሳበት ተስፋዬ ገ/አብ አሜሪካ ገብቶ የሚያናግረው ሚዲያ በማጣቱ “በሚዲያ ረሃብ” እየተሰቃየ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ በክፉም ይሁን በመልካም ከሚዲያ መገለል የማይወደው ተስፋዬ “ሻዕቢያን የሚያጋልጥ መጽሐፍ ጽፌአለሁና አናግሩኝ” እያለ በዳያስፖራ ያሉትን ሚዲያ እየለመነ፣ በራቸውን እያንኳኳ መሆኑ ተነግሯል - በተለይ የተንቀሳቃሽ ምስልና (TV and YouTube) የሬዲዮን፡፡ ዛጎል እንደዘገበው ከሆነ እስካሁን ዕድሉን የሰጠው የለም፡፡ ተስፋዬ ከዚህ በፊት እየጻፈ የሚያወጣቸው መጣጥፎች እንደዱሮው ተነባቢነት ካጡ ሰነባብተዋል፡፡ የኦሮሞም ጽንፈኞችም እንደፈለጉ ሲጠቀሙበትና እሱም በተራው ሲጠቀምባቸው ቆይቶ አሁን ከእርሱ “የተሻሉ” አግኝተው ትተውታል፡፡ በርካታ እርሱን የሚተኩ … [Read more...] about ተስፋዬ ገ/አብ “የሚዲያ ያለህ” እያለ ነው!
ክንፉ ምን ነካህ?
ቴዲ በክርስቶስ ተቦርነም በጲላጦስ እንዲት ይመሰላሉ? ምሳሌያዊ አነጋገሮች ተረቶቻች፣ የታላላቅ ሰዎች አባባሎች መጽሐፍትና ገጠመኞች እየተጠቀሱ ንግግር መክፈቻም ሆነ የጽሁፍ መነሻ መሆን በፊትም የነበረ አሁንም የቀጠለ የተለመደ ነገር ነው። እንደዚሁም የክርስቶስ ቃል የሀዋርያት ትንቢት ምሳሌና ተግሳፅም እንደቦታው አስፈላጊነት የሚጠቀስበት ጊዜ አለ። ይህም የሚሆነው ትምህርት ለመስጠት የእግዚአብሔርን ቃል ለመስበክ እንደአስፈላጊነቱም ጊዜውና የተፈጸመውን ድርጊት ለማስተማር ነው። በሰርግ ጊዜ ጌታ በሰርግ ቦታ ተገኝቶ ባዶዎቹን እንስራዎች በጣፋጭ ወይን ሞላቸው ተብሎ ትምህርት እንደሚሰጠው። አንተም ለጽሁፍህ መነሻ ያደረከው ቃል በማትዮስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፯ ቁጥር ፲፩. ሰፍሮ ይገኛል። ቃሉም እንደሚያስረዳው እየሱስ በዛን ጊዜ ይሁዳ አሳልፎ ስጥቶት ሽማግለዎችና የካህናት … [Read more...] about ክንፉ ምን ነካህ?
US Lobbying Firm (SGR) Cozy with a Ruthless Dictatorial Regime in Ethiopia For 1.8 Million Dollars
Lobbying Firms in the US are known to represent big corporations like oil, construction, food manufacturing and pharmaceutical industries, trying to persuade lawmakers to support business friendly legislations. As this is a controversial practice, politicians running for office do not want to be associated with Lobbying firms. In fact, it was a major discussion topic during the 2016 presidential election season for both candidates. The main reason for politicians to discredit lobbying firms … [Read more...] about US Lobbying Firm (SGR) Cozy with a Ruthless Dictatorial Regime in Ethiopia For 1.8 Million Dollars
የትግራይ ብሄርተኞች ዕብሪትና የጣናው ሞገድ ፈተና በመቀሌ!
“የትምክህት ፈረስ፣ ነፍጠኛ፣ የምኒልክ ርዝራዥ፣ አማራ አህያ፣ ገና መቶ ዓመት እንገዛሃለን፣ …” የመቀሌ ከነማ ደጋፊዎች ጭፈራ “የሌባ አይነ ደረቅ መልሶ ልብ ያደርቅ” የባህርዳር ከነማ ደጋፊዎች የመልስ ጭፈራ የመጨረሻው መጀመሪያ ይሆን? ያስፈራል! በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውድድር ከፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ቀጥሎ የከፍተኛ ሊግ ጨዋታዎች የተለየ ትኩረት ይስባሉ። የከፍተኛ ሊግ ጨዋታዎች ወደ ፕሪሚየርሊግ ለማደግ የሚደረጉ ፍልሚያዎች በመሆናቸው የተመልካቾችን ቀልብ ይስባሉ። የከፍተኛ ሊግ ጨዋታዎች ምድብ “ሀ” ላይ የተደለደሉት ክለቦች በወጣላቸው መርሐ-ግብር መሰረት ግንቦት 5 ቀን 2009 ዓም በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ጨዋታቸውን አድርገዋል። የዚህ ውድድር ተሳታፊ የሆኑት መቀሌ ከነማ እና ባህርዳር ከነማ (የጣናው ሞገድ) በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስ ግቢ (FB campus) … [Read more...] about የትግራይ ብሄርተኞች ዕብሪትና የጣናው ሞገድ ፈተና በመቀሌ!
የጃንሆይ እናት!
ነገሩ ትንሽ ቆየ። እኔ ግን በሆነ አጋጣሚ በቅርቡ ነው ቃለ ምልልሱን የሰማሁት። ተስፋዬ ገብረአብ አዲስ ስላሳተመው - “የጀሚላ እናት” መጽሃፍ፤ ከጋዜጠኛ በፍቃዱ ሞረዳ ጋር አጭር ቃለ ምልልስ አድርጎ ነበር። በትክክል እንዳዳመጥነው ከሆነ፤ “የቀዳማዊ ኃይለስላሴ እናት ስም ጀሚላ ነው፤ አንድ ወገናቸው ስልጤ ጉራጌ ነው - በሌላ ወገን ኦሮሞ ናቸው።” ይለናል። በመቀጠልም፤ “የጀሚላ እናት በአቶ በዛብህ ተጠልፈው ነበር። አቶ በዛብህ ከምኒልክ ጋር በጦርነት ሞቱ። የቀዳማዊ ኃይለስላሴ ወይም የጀሚላ እናት እልፍኝ ውስጥ፤ በአጼ ምኒልክ ተገደሉ።” የሚሉና ሌሎች ተዘርዝረው የማያልቁ የልብወለድ ነገሮች በመጽሃፉ ውስጥ ማካተቱን በቃለ ምልልሱ ላይ ሰማን። ወደ ኋላ በመመለስ ‘በወቅቱ ምላሽ የሰጠ ሰው ይኖር ይሆን?’ በማለት አንዳንድ ድረ ገጾችን ብመለከት፤ በዚህ የተዛባ ታሪክ ምክንያት… … [Read more...] about የጃንሆይ እናት!