ሟች - ሊደፍራቸው የመጣ ሳውዲ ወጣት ገዳይ - ሚስትና ቤቱን የተከላከለ ጎልማሳ ፍርድ ሰጭ - ከፍተኛው የሸሪአ ፍርድ ቤት የወንጀል ችሎት እነ ሁሴን እንደገና አልተወለዱ ይሆን? ልክ የዛሬ 3 ዓመት ገደማ ሳውዲ አረቢያ ጅዳ "ሀበሾች ሳውዲ ገደሉ!" ተባለ፣ መረጃውን የሰማሁት እኔም በእስር ላይ እያለሁ ነበር። እንዴት ገደሉ ብየ ስጠይቅ ቤታቸውን ሊዘርፉና የሀበሻውን አባወራ ቤት ሊዘርፉ የገቡ ሳውዲ ወጣቶች ሴቶችን ሊደፍሩ በተነሳ አምባጓሮ መሆኑን በደፈናው ሰማሁ። ከዚያም የቀረውን ተባራሪ የእስር ቤት መረጃ የማጣራበት መንገዱ ዝግ በሆነበት የጨለማ ወቅት ገደሉ የተባሉት ወደሚታጎሩበትና እኔ ወዳለሁበት ወህኒ እስኪመጡ የታሳሪውን ተባራሪ የማያጠግብ መረጃ ሳነፈንፍና ስኮመኩም ከረምኩ። ከሶስት ወር በኋላ እኔ ከወህኒ እስክወጣ ወደ ማዕከላዊው የብሪማን እስር ቤት … [Read more...] about ሰው ገድለው አንገታቸው ሊቀላና ሊያሳዝኑን የነበሩት በነጻ ተለቅቁ!
Archives for March 2017
ስለአደዋ ስለምኒልክ በስዊድን
እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር ማርች ፩፯ ፳፩፯ በኢትዮሚድያ ድህረ ገፅ ላይ በወጣ ፅሁፍ ላይ ወለላዬ ከስዊድን የተባሉት ፀሀፊ “እምዬ ምኒልክ ወላዋይ ነበሩ ወይ?” ሲሉ አበክረው ይጠይቃሉ። በፅሁፉ መሃልም ወለላዬ ጋዜጠኞችና ተመራማሪዎች የትናቹ፤ ዝም አትበሉ ሲሉ ይማፀናሉ። የጥሪያቸው ምክንያትም የስዊድን ሶሻል ዴሞክራት ተቀጥላ የሆነው የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራት ማኅበር የአድዋን ድል በዓል ምክንያት በማድረግ ማርች ፭ ቀን ፳፩፯ ባዘጋጀው ዝግጅት ላይ የመጨረሻው ተናጋሪ ያደረጉት ንግግር ነበር። እኝህ ሶስተኛ ተናጋሪ ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ ይባላሉ። በድህረ ገፅ ላይ የሚገኝ መረጃ እንደሚያሳየው ፕሮፌሰር ተከስተ አስመራ ኤርትራ የተወለዱ ብዙውን ዘመናቸውን ደግሞ ስዊድን ውስጥ በታሪክ መምህርነትና ፀሀፊነት የሰሩ ሰው ናቸው። ብዙዎቹ የጥናት ፅሁፎቻቸውም በኤርትራ የቅኝ ግዛት ታሪክ ላይ … [Read more...] about ስለአደዋ ስለምኒልክ በስዊድን
አድዋን ወደ ፖለቲካ ድል መቀየር ለምን ተሳነን? እርግማን ሦስት “ምኒልክ የእኛ ነው”
ከዝግጅት ክፍሉ:- “አድዋን የሚያህል ወታደራዊ ድል ስለምን ወደ ፖለቲካዊ ድል መቀየር ተሳነን?” በሚል ርዕስ ተከታታ ጽሁፎች ስናትም ሰንብተናል፡፡ የመጀመሪያው ክፍል ሙሉ ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡ እርግማን ሁለት “ሚኒልክ ኤርትራን ሸጠ፤ ትግራይን በደለ” የሚለው ሁለተኛው ክፍል ደግሞ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ በሦስተኛው ክፍል የመጨረሻውንና ማጠቃለያውን ይዘን ቀርበናል፡፡ አፄ ምኒልክ ባልዋለበት ማዋል የዘመናችን “ፖለቲከኞች” ከታሪክ የሚያገኙት ግብር - አልባ ትርፍ ሆኗል፡፡ የአፄውን አገር የማቅናትና የግዛት አንድነትን የማስከበር ዘመቻ በ“ቅኝ ግዛት” የሚተረጉሙት እንዳሉ ሁሉ የማዕከላዊ መንግስት መቀመጫ ከትግራይ ወደ ሸዋ በመዞሩ ምኒልክን “ባንዳ” እና “አገር ሻጭ” እያሉ የአባቶቻቸውን ዝንፈት በአደባባይ ምኒልክ ላይ የሚለጥፉ ብልጣብልጥ “ፖለቲከኞች” … [Read more...] about አድዋን ወደ ፖለቲካ ድል መቀየር ለምን ተሳነን? እርግማን ሦስት “ምኒልክ የእኛ ነው”
እምዬ ምኒልክ ወላዋይ ነበሩ ወይ?
የአድዋን በዓል አከብራለሁ ብዬ ሄጄ፤ አፄ ምኒልክ ሲሰደቡ ሰምቼ ተመለስኩ ምሁር ባልባልም በቃ! አልጸጸትም፣ ፊደል ቢሸከሙት አያደርስም የትም። አሮጌ ልብስ ነው አስቀያሚ ኮተት፣ ማስተዋል ካነሰው ቢከመርም ዕውቀት። (የረቡዕ ግጥም ፫ኛ ዓመት፣ ወለላዬ) የስዊድን ሶሻል ዴሞክራት ተቀጥላ የሆነው የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራት ማኅበር የአድዋን ድል በዓል ምክንያት በማድረግ ዝግጅት አድርጎ ነበር፤ እሁድ ማርች 5 ቀን 2017። በዝግጅቱ ላይ እንድገኝ ጥሪ ደርሶኝ ከተካፈሉት ጥቂት ሰዎች መካከል አንዱ ነበርኩ። ዝግጅቱ በቪድዮ ክሊፕ እንድናዳምጣቸው የተመረጡልን ሰዎች ሲኖሩት፣ በአካል የተገኙ እንግዳም ነበሩ። ክሊፑን በስክሪን እያየን ካዳመጥናቸው አንዱ “The Battle of Adwa” የተባለውን መጽሐፍ የጻፉት ፕሮፌሰር ዮናስ ሬይሞንድ ሲሆኑ፣ ስለ መጽሐፋቸው ከኢጣሊያ የታሪክ … [Read more...] about እምዬ ምኒልክ ወላዋይ ነበሩ ወይ?
የሕይወት ዋጋ – “አጥንታቸውን እሾህ ያርገው”
በ2009 ዓ.ም. ቆሼ የሚባል ሰፈር ወይም መንደር ተፈጠረ፤ ቆሼ ማለት ቆሻሻን ማቆላመጫ ነው፤ ቆሻሽዬ ማለት ነው፤ ቆሼ የቆሻሻ ተራራ ነው፤ በዚያ የቆሻሻ ተራራ ዙሪያ መሄጃ የሌላቸው ሰፈሩበት፤ ጥንት ሴትዮዋ እንዳለችው፡- እሾህ ብቻ ሆነ እግሬን ብዳብሰው እንዴት መራመጃ መሄጃ ያጣል ሰው! ሴትዮዋ ይህንን ያንጎራጎረችው ከብዙ ትውልዶች በፊት ነው፤ ጉልበተኞች የኢትዮጵያን ሰዓት ሰንገው ስለያዙት አይነቀነቅም! ባለህበት ሂድ! ነው፤ ዛሬም መሄጃ የለም፤ ቆሻሻንም የሙጢኝ ቢሉ ማምለጥ አይቻልም፡፡ እነዚህ አንድ መቶ አሥራ ሦስት ሟቾች በርግጥ ሰዎች ናቸው? በርግጥ ኢትዮጵያን ናቸው? የምናገረው ጠፍቶኛልና ጥያቄዎች ብቻ ልጠይቅ፡-- ቤታቸውን ጉልበተኞች አፍርሰውባቸው፣ መሬታቸውን ሰማይ-ጠቀስ ወይም መንገድ ለመሥራት መሬታቸውን ወስደውባቸው የሚደርሱበት አጥተው፣ ባዶ ቦታ ፈልገው … [Read more...] about የሕይወት ዋጋ – “አጥንታቸውን እሾህ ያርገው”
ነጠላ ተባራይ ንፍቅ ስነ-ስሌት [ካልኩለስ በአማርኛ]
ይህ መፅሀፍ ለፊዚክስ ሂሳባዊ ዝግጅት በሚል በኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርስቲ ፕረስ የታተመው የጥራዝ ፩ ተከታይ በመሆን፣ ለሳይንስ እና ምህንድስና ትምህርት ኣገልግሎት ተጨማሪ ሂሳባዊ ፅንስ-ሃሳቦችን ይሰጣል። ስለሆነም፣ በቅድሚያ ኣጭር ኣልጀብራዊ (Algebraic) እና ስነ-ዘዌያዊ (Trigonometric) ክለሳ ከሰጠ በሁዋላ፣ ስለ”ተግባር” (Function) በሰፊው ያብራራል። ቀጥሎም፣ ዋና የስነ-ስሌት መሰረት በሆነው ለከት (Limit)፣ ስነ-ቅርፅ (Geometry) እና የቀጥተኛ መስመር ዝንባሌ (Slope) በመጠቀም የ”ለውጥ ቅልጥፍና” (Rate of Change) እና ለማንኛውም የተግባር ዝብ (Curve) ዝንባሌ የሚያገለግለውን በስነ-ስሌት ድናን (Derivative) በመባል የሚታወቀውን ያብራራል። የድናን ኣጠቃቀም እና ፋይዳን በተለያዩ የትምህርት ቅርንጫፎች ያሳያል። ለዚህም፣ ከሁለት … [Read more...] about ነጠላ ተባራይ ንፍቅ ስነ-ስሌት [ካልኩለስ በአማርኛ]
ድንቄም ሀዘን!
ሲሉ ሰምታ ዶሮ ሞተች ከቋት ገብታ ይሉ ነበር ሳይማሩ የተማሩት ጠቢባን የሆኑ ቀደምት እናትና አባቶቻችን። ድህነት ዛዝላውን ጭኖባቸው የመከራ ኑሮ የነበሩ ወገኖቻችንን መንግስት የቆለለው የቆሻሻ ምርት ተጭኗቸው ሲያልቁ መንግስት የሶስት ቀን ሀዘን ተቀመጠ የሚል አስቂኝ ወሬ በሰማሁ ጊዜ ነበር የጠቀስኩት የዶሮዋ ምሳሌ ትዝ ያለኝ። ሀገር አለን ብለው እንደወግና ስርአታቸው አደባባይ ሊውሉ የወጡ ወገኖቻችንን ባልተደበቀ ሸር በቢሸፍቱ ከተማ እንደወጡ ያስቀረው መንግስት በወቅቱ የሶስት ቀን ሀዘን በማወጅ በሙታንም ህያዋንም ላይ ቀልዶ ነበር። እነሆ አሁን ደግሞ በከመረው ቆሻሻ ህፃናትና ስቶችን ጨፍልቆ ከፈጀ በኋላ ሳቂታውን ፓርላማ ሰብስቦ በሉ አሁን ደግሞ የሀዘን ሰአት ነው አለ አሉ። እንዴት ያለ ቀልደኛ መንግስት ነው ጃል? ለገደለው ህዝብ ሆዱ የሚባባ ሩሩህ መንግስት! የዚህ አይነቱ ቀልድስ … [Read more...] about ድንቄም ሀዘን!
የቆሻሻ ፖለቲካ ተምሳሌት – ቆሼ!! “ድህነት ዋናው ጠላታችን ነው”
የግፍ ክምር ናዳው ምን ያህል የሚከፋ ይሆን? አዲስ አበባ ቃላት የማይገልጹዋት፤ ስሟ ግብሯን የማይወክል የግፍ ከተማ ናት፡፡ በአንድ በኩል ሥጋ በል ለሆኑ የቤት እንሰሳዎቻቸው የዕለት ተዕለት ምግብ ከሱፐርማርኬት የታሸገ ሥጋ ገዝተው የሚመግቡ ባለጠጎች፤ በሚስታቸውና በልጆቻቸው እንዲሁም በደርዘን ውሽሞቻቸው ሥም የተንጣለሉ ቪላ ቤቶችንና ግዙፍ ህንፃዎችን የገነቡ የገዥው ኃይል ማኅበራዊ መሰረት የሆኑ የትግሪኛ ቋንቋ ተናጋሪ የከተማ ዘራፊዎች (Marauders’ city) “ወጋ ትበለይኪ” እያሉ የሚምነሸነሹባት፤ ደሃ-ገፊ መሐል አሟቂ፤ የቁስ ሰቀቀን የተጫናቸው የፖለቲካ-ኢኮኖሚ ዘዋሪ ልሒቃን ከተማ ናት፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የዕለት ምግባቸውን ከቆሻሻ ገንዳ የሚለቅሙ አንጀታቸው በረሃብ የታጠፈ ጐስቋላ ምንዱባን በጐዳና የሚኖሩባት፤ የወር ደመወዛቸውን ለአልቦ-አንጀት (ርህራሄ የለሽ!) … [Read more...] about የቆሻሻ ፖለቲካ ተምሳሌት – ቆሼ!! “ድህነት ዋናው ጠላታችን ነው”
ሕዝባዊ ናዳ ሊውጠው የሚገባ አገዛዝ
ቅዳሜ መጋቢት 2 ቀን 2009 ዓ.ም. ከምሽቱ ሁለት ሰዓት አካባቢ በአዲስ አበባ ደቡብ ምዕራብ ክፍል በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ በተለምዶ “ቆሼ ሠፈር” እየተባለ በሚጠራው ቆሻሻ ማጠራቀሚያ በደረሰው የመሬት መናድ አሳዛኝ አደጋ፣ የሕዝብ እልቂት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን ከ“አንድ ሀገር! አንድ ሕዝብ! ኢትዮጵያችን ሕዝባዊ ንቅናቄ” እንገልጻለን። የወያኔ አገዛዝ ሕዝባችንን ለኅሊና በሚዘገንን አኳያ በረሃብ እየቀጣ መሆኑ በተደጋጋሚ የተገለፀ ጉዳይ ነው። በመዲናችን አዲስ አበባ ህብረተሰቡ የዕለት ጉርሱን እንዳያገኝ በተለያየ መልኩ ይቀጣል። በየቤቱ ያለውን ረሃብተኛ ቤት ይቁጠረው። በቀን አንዴ ለመመገብ ያለውን እሩጫ የሚፈጋው ያውቀዋል። ወያኔ በተለይ ከ1997 ዓ.ም. የምርጫ ክስረት በኋላ የ“አዲስ አበባን ሕዝብ እንቀጣዋለን” እንዳለው አንዱ ጅራፉ ረሃብ ነው። ሆን ተብሎ … [Read more...] about ሕዝባዊ ናዳ ሊውጠው የሚገባ አገዛዝ
የማህበረሰብ ጠንቅነት ዝንባሌን እንዴት ማወቅና መጠንቀቅ እንችላለን?
ላለፉት በርካታ አመታት እኛ በውጭና በሀገር ዉስጥ የምንገኝ ኢትዮጵያውያንና ትዉልደ ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያውያ ዉስጥ የተሻለ መንግሥታዊ አስተዳደር እንዲመጣና ባጠቃላይ ፍትህ እንዲሰፍን ያላሰለሰ ጥረት ስናደርግ ቆይተዋል። ይሁን አንጂ በተለያዩ ተቆጥረዉ በማያልቁ ምክንያቶች፣ አብዛኞቹ ደግሞ እራሳችን በፈጠርናቸዉ ድክመቶች እስካሁን የከፈልናቸዉ መሥዋቶች፣ ድካማችንና ልፋታችን የታለሙለትን ያህል ግብ ሊመቱና ፍሬያማ ሊሆኑ አልቻሉም። በዚህም የተነሳ ብዙዎቻችን በመሰላቸትና በምሬት ይመስላል፣ ከዋናዉ ጠላታችን ከወያኔ ጋር ከመታገል ይልቅ ምሬትና ብስጭታችንን ስርዓቱን በሚደግፉ የዉጭ ሃያላን መንግሥታትና ባመዛኙ ደግሞ ኃይላችንን እርስ በርሳችን በመነታረክ ላይ እያባከንን እንገኛለም (ተጠምደናል)። ከዚህ በፊት ስንጓዝበት ከነበረዉ የተሳሳተ ጉዞ ሳንማር አሁንም የቀድሞ ስተታችንን … [Read more...] about የማህበረሰብ ጠንቅነት ዝንባሌን እንዴት ማወቅና መጠንቀቅ እንችላለን?