ዓይኔን በዓይኔ ያየሁበት፣ በስተእርጅና ያገኘሁት፣ የትናንቱ ማሙዬ፣ ያሳደኩት አዝዬ የንግሊዞችንወረራ ሰምቶ፣ በቴዎድሮስ ሞት ተቆጥቶ፣ ለምን? ለምን ሞተ? ብሎ ሲያለቅስ፣ የዓይኑን ዕንባ ላደርቅ- የልቡን መሰበር ላድስ፣ ጀግኖቻችንን ቆጥሬ- ታሪካችንን ባወድስ፣ ዕንባውን ዋጥ አድርጎ- በአትኩሮት ዓይኔን እያየኝ፣ «አንተስ...?» አንተስ!- ምን ሰርተሀል? በማለት ጠየቀኝ። እድሜ ቢደራረብ ተግባር ሳይላበስ፣ እንደዚህ እንደኔ ያስጠይቃል ለካስ! (ወለላዬ) … [Read more...] about “አንተስ…?”
Archives for February 2017
የድርድር ቅድመ ጸብ “በተቃዋሚዎች” መካከል እና የጠብ-መንጃ “ሰላም” እስከመቼ?
ቅድሚያ "የታሰሩ ይፈቱና አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ይነሳ" የሚለው ኢህአዴግን ሳይሆን “ተቃዋሚዎችን” አላስማምም፤ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች "ቅድሚያ ይፈቱ" የማያስማማቸው ተቃዋሚዎችን አንድ የማድረግ ሃሳብም አለ። ይህንን ሃሳብ የሚያራምደው ደግሞ ኢዴፓ ነው። የህብረቱን ጥያቄ በፕሮግራም ደረጃ አርቅቆ በይፋ ጥሪ ያቀረበውን ኢዴፓ ተቃዋሚዎች የሚያቀርቡትን ቅድመ ሁኔታ አይደግፍም። ይህንኑ ተከትሎ ኢዴፓ በኢህአዴግ ይደገፋሉ ተብለው ከሚታሙትና የቤተሰብ ጥርቅም የሆኑትን ካልሆነ በዚህ አቋሙ ያሰበውን ሊያሳካ እንደማይችል አስተያየት እየተሰጠ ነው። ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የፖለቲካ አካሄድ እንደተቀየረና ከቀድሞው ይልቅ እየከረረ መሄዱን ሁሉም ወገኖች ይስማሙበታል። በደጋፊና ተከታይ ብዛት ተጽዕኖ ፈጣሪ ወይም ተሰሚነት አላቸው የሚባሉት የብሄር ፓርቲዎች ይህንን የከረረውን … [Read more...] about የድርድር ቅድመ ጸብ “በተቃዋሚዎች” መካከል እና የጠብ-መንጃ “ሰላም” እስከመቼ?
መስጊዳቸው ለተቃጠለባቸው የአይሁድ ቤተመቅደስ ቁልፍ ተሰጣቸው
በቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት በቪክቶሪያ ከተማ መሰጊዳቸው ለተቃጠለባቸው ሙስሊሞች በከተማዋ የሚገኘው የአይሁድ ምኩራብ በሩን ከፈተላቸው፡፡ እንደ ሲኤንኤን ዘገባ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ በቪክቶሪ ቴክሳስ የሚገኘው እስላማዊ ማዕከል (መስጊድ) ቃጠሎ ደርሶበት ነበር፡፡ ይህንን የተመለከቱ በከተማው የሚገኘው የአይሁድ ማኅበረሰብ አባላት የአምልኮ ቦታቸውን ለሙስሊም ወገኖቻቸው መሰብሰቢ እንዲጠቀሙበት የምኩራባቸውን ቁልፍ ሰጥተዋቸዋል፡፡ “አሁን ያገኘነውን ዓይነት ዕርዳታና ድጋፍ አናገኝም ብዬ በፍጹም አልተጠራጠርኩም” ያሉት የእስላማዊ ማዕከሉ ፕሬዚዳት ዶ/ር ሻሒድ ሐሽሚ ናቸው፡፡ እንደ እርሳቸው የቀዶ ጥገና ባለሙያና የአይሁድ ቤተመቅደስ አባል የሆኑት ዶ/ር ጌሪ ብራንፍማን ወደ ዶ/ር ሻሒድ ቤት በመሄድ ቁልፉን አስረክበዋቸዋል፡፡ መስጊዱን እንደገና ለመሥራት ከዘጠና … [Read more...] about መስጊዳቸው ለተቃጠለባቸው የአይሁድ ቤተመቅደስ ቁልፍ ተሰጣቸው
ላንዲት መስቲካ ሻጭ ህጻን
በደብተርሽ ምትክ ትንሽ ሱቅ ታቅፈሽ ካልፎሂያጅ እግር ስር፤ እንደ ድንቢጥ ከንፈሽ ጋሼ ግዙኝ ስትይ፤ ኣንጋጠሽ ወደ ላይ ለጉድ ተጎልቸ፤ ምታረጊውን ሳይ ራሴስ ይታመም፤ ምላሴን ምን ነካው ግራዋ ይመስል፤ መረረኝ ማስቲካው:: ኣፈር ጠጠር ለብሶ ፤በዶዘር ተድጦ መስኩ ከነጎርፉ ሰማይ ከነዶፉ ለጌቶች ተሽጦ ኣተር ነው እያሉ፤ ኣፈር ዘግኖ መፍጨት ገነት ነው እያሉ፤ መስክ ላይ መፈንጨት ጠበል ነው እያሉ፤ ተጎርፉ መራጨት ይህንን ማን ሰጦሽ ገና በልጅነት፤ ልጅነት ኣምልጦሽ፡፡ በምቢልታ በዋሽንት፤ በከበሮ ታጥሮ በክራር ተማግሮ በቆመ ከተማ እምባሽ ቅኝት የለው ፤ለሰው ኣይሰማ፡ ጠዋት የፎከረ ፤ቀትር ላይ ሲረታ ዛሬ ዝሎ ሲወድቅ ፤ትናንት የበረታ ኑሮን ያህል ሸክም፤ ያላንቀልባ ሲያዝል፡፡ ምን ጸጋ ለብሶ ነው፤ ትከሻሽ የማይዝል፡፡ (በእውቀቱ … [Read more...] about ላንዲት መስቲካ ሻጭ ህጻን
ፕ/ር ኃይሌ ላሬቦ እና “የቁቤው ትውልድ” ፖለቲካ
ለሰሞኑ ግርግር መንስኤ የሆኑት ፕ/ር ኃይሌ የተጠቀሟቸው ሁለት ቃላት ናቸው ተብሏል። "ጋላ" እና "እረኛ" የሚሉ ቃላት። በኢትዮጵያ የታሪክ መዛግብት ውስጥ እነዚህ ቃላት "ሰፍረዋል" ወይንስ "አልሰፈሩም" የሚለውን ጉዳይ ለግዜው እንተወው። ፕሮፌሰር ኃይሌ ላሬቦ በቃለ-መጠይቁ እነዚህን ቃላት መጠቀማቸው "ስህተት ነው" ወይንም "ስህተት አይደለም" ወደሚለው ትንታኔም አልገባም። እነዚህን ጥያቄዎች ለታሪክ ለተመራማሪዎቹ ልተውላቸው። ፕሮፌሰሩ ከወንድማገኝ ጎሹ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ እነዚያን ቃላት ባይጠቀሙስ፣ ከስድብ እና ከአድማው ይድኑ ይሆን? የሚለው ጥያቄ ግን ትንሽ ወደ ኋላ እንድዞር አድርጎኛል። "ዳግማዊ ምኒልክና ታሪካዊ ክንውኖቻቸው" በሚል ርዕስ አንጋፋው ጋዜጠኛ ተክሌ የኋላ ከሁለት አመት በፊት ሦስት እንግዶችን በጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ጋብዞ አወያይቷቸው ነበር። … [Read more...] about ፕ/ር ኃይሌ ላሬቦ እና “የቁቤው ትውልድ” ፖለቲካ
ጻዕረ ሞትና መስፍን ወልደ ማርያም
አንደኛ፣ ገና በልጅነቴ አሥር ዓመት ግድም ሲሆነኝ አንድ በድቀድቂት ከእንጦጦ ወደታች የሚወርድ ኢጣልያዊና እኔ ተጋጠምን፤ እሱ በዚያ በጥቁር ድንጋይ ኮረት በረበረበበት መንገድ ላይ ሲጓዝ ወደ እንጦጦ የሚወጣ ወታደሮችን የጫነ ከባድ መኪና ቆሞ ነበር፤ በዚያ መኪና ላይ አንድ ዝንጀሮ ነበር፤ የኔ አትኩሮት በዚህ ዝንጀሮ ላይ ነበር! እንደሚመስለኝ ዝንጀሮውን እያየሁ ስሮጥ ከድቅድቂቱ ጋር ተገናኘን፤ እኔ ከስር በተረበረበው የጥቁር ድንጋይ ኮረት ላይ፣ ድቅድቂቱ ደግሞ የእኔን ራስ ጨፍልቆ! ምኒልክ ሀኪም ቤት ከስንት ቀኖች በኋላ የካቶሊክ መነኮሳት አስታማሚዎች ከነመለዮአቸው አልጋዬ አጠገብ ቆመው በትልቅ የበሽተኞች ድንኳን ውስጥ በአንዱ መደዳ ውስጥ ተኝቼ ነቃሁ፤ መድኃኔ ዓለም ማንን ልኮ የእኔን ጭንቅላት ከድንጋዩና ከድቅድቂቱ መክቶ እንዳዳነኝ አላውቅም፡፡ ሁለተኛ ከሶደሬ መውጫ ላይ በመቶ … [Read more...] about ጻዕረ ሞትና መስፍን ወልደ ማርያም
“ኮከብ ባየሁ ቁጥር እበረግጋለሁ” ዘ-ሃበሻ እግዜር ይይልሽ!
ከሶቅራጥስ ዘመን ጀምሮ ሲነገር የኖረውን “እውቀት እና መረጃ ሃይል መሆኑን” መንገር፣ እንዲሁም “...መረጃን መገደብ... የአምባገነኖች እና ህዝብን የሚበዘብዙ እና የሚጨቁኑ ...” ገዢዎች ስራ መሆኑን መጻፍም፣ አንባቢህን አለማወቅ/መናቅ ቢሆንም፣ ክፋት የለውም። “...መረጃዎች እንዳይወጡ ማድረግ የጨቋኞች ባህሪ ነው....”፣ በሚል መንደርደሪያ ተነስቶ፣ ከ“ጨቋኞች” የተጻፈ መሆኑን ለማሳየት/ለማጋለጥ አንድም ሃርግ መዘው ሳያወጡ እና ሳይተቹ፣ ባለፈው የለቀቅሁትን ጽሁፍ “የጨቋኞች ጽሁፍ ... የመንደርተኛ ወሬ ነው...” ማለት አግባብ አይደለም። ጽሁፉ፣ ሙያዊ ግምገማ/ትችት እንኳን ባይመስላቸው “ከጨቋኞች የመጣ ነው” ማለቱ ራሱ፣ የዘሃበሻን ኢዲቶሪያል ቦርድ ትዝብት ላይ ይጥላል። በመሰረቱ ከ“ጨቋኝ” ጋር እየታገልን ነው ማለታቸውም ነው። የዘሃበሻ “ኢዲቶሪያል ቦርድ”፣ ጋዜጠኝነት … [Read more...] about “ኮከብ ባየሁ ቁጥር እበረግጋለሁ” ዘ-ሃበሻ እግዜር ይይልሽ!
“የተቆለፈበት ቁልፍ” በቃላት ቁልፍ ተቆላልፏል!
ለረጅም አመታተ የጣልኩትን ብዕር ድር ካደራበት ሰገባው እንድመዝ አስገደደኝ - በ ኢትዮ-ሚዲያ (Ethiomedia) እና በጎልጉል (Googlgule) ድህረ-ገፆች ላይ ከወራት በፊት በዶክተር ፍቃዱ በቀለ በተባሉ ግለሰብ በ"የተቆለፈበት ቁልፍ" መፅሐፉ ላይ የቀረበ አንድ ፅሑፍ። "ሃያሲው" በዘመናችን አቻ ያላገኙለት (ወደር የሌለው) መፅሐፉ መሆኑን ነው የገለፁልን። "...የስነ-ጽሁፍም ዋና ዓላማው በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ያሉትን አስቀያሚም ሆነ ቆንጆ ነገሮች ስዕላዊ በሆነ መልክ መግለጽ ሲችሉና አንባቢውን በልዩ ሃሳብ ውስጥ ተመስጦ እንዲዋኝ ማድረግ ሲችሉ ብቻ ነው።..." በማለት ካብራሩ በኃላ ከ`ዚህ አንፃር "የተቆለፈበት ቁልፍ" እንደተዋጣለት መሰክርነታችውን ይሰጣሉ። አንዲህ ሲሉ "....በታሪካችን ውስጥ በመጀመሪያ ጊዜ በልዩ አቀራረብ የተዘጋጀና የተጻፈ ትምህርታዊ መጽሀፍ ነው … [Read more...] about “የተቆለፈበት ቁልፍ” በቃላት ቁልፍ ተቆላልፏል!
“እኩል ደራ ደራ ከነ‘ሜቴ ጋራ!”
ገጣሚና ደራሲ... ከግዑዙ መሬት፣ ከመንደሩ ይልቅ ከዘር ማንዘሩ፣ ሰብዓዊነትን ያልማል ብዕሩ “የሰው ልጅ ልብ...” ነው አገሩና ድንበሩ! ሰብዓዊነት ነው ክብሩ፤ ገጣሚ አገር የለውም፣ “ዩኒቨርሱ”ም አይበቃውም፤ ሰዋዊ ህመም ያመዋል፣ ፈውሱም ይፈውሰዋል፣ ገጣሚ ያ ይበቃዋል! ወርዶ ወርዶ “ቀየ መንደር ውስጥ አይወድቅም” አዎ! ገጣሚ፣ ደራሲ እንዲያውም አገር የለውም፣ የበዓሉ አገሩ ሰው ነው፣ “...ህንጻው ምን ቢረዝም፣ ምን ቢጸዳ ቤቱ፣ መንገዱ ቢሰፋ ቢንጣለል አስፋልቱ፣ ሰው ሰው ካልሸተተ ምንድነው ውበቱ፣ የኔ ውብ ከተማ የኔ ውብ አገር፣ የሰው ልጅ ልብ ነው የሌለው ድንበር...” (ኦሮማይ) ጸጋዬም ጊንጪ ኢምንት ቢሆንበት ጉደር፣ አምቦ፣ ቡራዩ ... ጠ’ቦበት፣ አዲሳ’ባ ኢትዮጵያም ብታንስበት፣ ብዕሩ ፈርዖኦንን ተመኘ፣ ነፈርቲቲ እና አፍሮዳይትን … [Read more...] about “እኩል ደራ ደራ ከነ‘ሜቴ ጋራ!”