ከኢትዮጵያ ሕዝብ ብሔራዊ ፓርቲ ለጦር ሃይሎች የቀረበ ጥሪ ዘረኛው የወያኔ/ኢሕአዴግ ቡድን ላለፉት 25አመት ሀገር በመከፋፈልና ሕዝብን በመግደል የፈፀመው እልእቂት አነሰ ብሎ አሁን ከሰሜን ሸዋ እስከ ጎንደር ክፍለ ሃገር ባለው ወገናችን ላይ የፈፀመው የዘር ማጥፋት አላማውን እያፋጠነ ነው። ለዚህም እውን ማስረጃው በየጊዜው ከሚያወጣው መግለጯወችና አዋጆች መገንዘብ ይቻላል። ይህ አልሞት ባይ ድርጊት የመጨረሻ ውእሳኔአቸው በመሆኑ ለአጋዚ ወታደሮቻቸው ለሰው ልጆች ሕሊና የሚቀፍና የሚሰቀጥጥ ትእዛዝ በተግባር እንዲፈፀም አስተላልፏል። ከዚህ አዋጅ በመነሳት ባለፉት ጥቂት ሳምንታት በሰሜን ክፍለ ሃገራትና በአዲስ አበባ ውስጥ አሮጊት ሽማግሌ ወጣትና ሕፃናት በተገኙበት አካባቢ እሳት በማጋየትና በእስር ቤት የሚገኙ ወገኖቻችንን እንዲሁም የከተማ ነዋሪዎችን የጥይት መለማመጃ አድርገዋቸዋል። … [Read more...] about ከኢትዮጵያ ሕዝብ ብሔራዊ ፓርቲ ለጦር ሃይሎች የቀረበ ጥሪ
Archives for September 2016
#ተቃውሞ #እምቢተኝነት #ተጋድሎ
እንባ እንባ ይለኛል ይተናነቀኛል እንባ ከየት አባቱ ደርቋል ከረጢቱ: ሳቅ ሳቅም ይለኛል ስቆ ላይስቅ ጥርሴ ስቃ እያለቀሰች መከረኛ ነብሴ:: (በአሉ ግርማ “ኦሮማይ”) ምነው! ፈጣሪ አምላክ! አላለቅስም ያልኩት ... እንባ የፈሪ ነው ብዬ ዋጥ ያ’ረኩት፣ አይቻል ተችሎኝ ይዤው የከረምኩት፣ ገንፍሎ ወጣና እንባዬ ፈሰሰ ጉንጮቼን ሰንጥቆ ፌቴን አዳረሰ በዛ እንባዬ መሀል አንገቴን አቅንቼ ለፈጣሪ ጮኽኩኝ! እጆቼን ዘርግቼ ምነው? ፈጣሪ አምላክ ምነው! ረሳኸን ምነው! ይሄን በደል አላይልን አልከን ምነው? የኛን ጩኸት ሰምተህ ጨከንክብን ብዬ ወተውትኩት አልኩበት እዬዬ አሁንም ይፈሳል አልቆመም እንባዬ ምነው! ፈጣሪ አምላክ! ... ወለላዬ የዛሬ 25 ዓመት ህወሃት የጀመረው በዚህ ነበር - … [Read more...] about #ተቃውሞ #እምቢተኝነት #ተጋድሎ
ሙስናውና የሕዝብ አመፁ በኤኮኖሚው ላይ እያደረሰ ያለው ጣጣና መኮታኮት
ዶ/ር ሰይድ ሃሰን (መሪ ስቴት ዩኒቨርሲቲ) መስከረም 1፣ 2009 በሲንሲናቲና አካባቢዋ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ያቀረቡት አጭር የንግግር ንጥረ ሀሳብ (ተቀርፎ የወጣ) የንግግሬ ንጥረ ሀሳቦች በ4 ይከፈላሉ፡ በኢትዮጵያ የተከሰተው ሙስና ምን ይመስላል? እንደትስ ማስወገድ ይቻላል? ሙስናው በኤኮኖሚው ላይ ያመጣው ክስረት፤የሙስና ንቅዘት የሕዛባዊ አመፁ አንዱ ምክንያት መሆኑ፤ የህዝባዊ አመፁ በኤኮኖሚው ላይ እያደረሰ ያለው ክስረት፤ ከኛ (ከዲያስፖራው) ምን ይጠበቃል? ሀ) በኢትዮጵያ የተንሰራፋው የሙስና ንቅዘት ጠባይ ምን ይመስላል? የኢትዮጵያን ሙስና በሚመለከት በርከት ያሉ ጽሁፎችንና ንግግሮችን አድርጌአለሁ። በዚህ ጉዳይም እቀጥላለሁ። በኢትዮጵያ ኢላይ ተንሰርፍቶ ያለው ሙስና ተመሳሳይነቱ በዩክሬይን፤ በራሽያና ተመሳሳይ ሀገሮች የተከትሰተውን አይነት … [Read more...] about ሙስናውና የሕዝብ አመፁ በኤኮኖሚው ላይ እያደረሰ ያለው ጣጣና መኮታኮት
የዐማራው ነገድ የጅምላ ፍጅትና ተጋድሎ ማስረጃዎች በከፊል!
ዐማራው ከ1972 እስከ 2008 ዓም ባሉት ዓመታት በዘረኛው የትግሬ ወያኔ በጠላትነት ተፈርጆ ከፍተኛ የሆነ የዘር ጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል የተፈጸመበት መሆኑን ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ባለፉት አራት ዓመታት ተከታታይ መግለጫዎችን ማውጣቱ ይታወሳል። በዚህም መሠረት በአጠቃላይ በወያኔ የዘር አገዛዝ ከ5 ሚሊዮን በላይ ዐማሮች ከምድረ-ገጽ እንዲጠፉ ተደርጓል። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ፣ ከዐማራው የጸዱ አካባቢዎችን ለመፍጠርና ዐማራውን አሰቃይቶ፣ አደህይቶና ከሰው በታች አድርጎ ተዋራጅ ለማድረግ ሀብት ንበረታቸውን በመንጠቅ ተባረዋል። አያሌዎች ለእስርና ለእንግልት ተዳርገዋል። በብዙ መቶ ሺዎች የሚቆጠሩ እንዲሰደዱ ተደርጓል። (ፎቶዎቹንና ዘገባውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about የዐማራው ነገድ የጅምላ ፍጅትና ተጋድሎ ማስረጃዎች በከፊል!
የአውሮጳ ኅብረት ድጎማ ህወሃት ኮሮጆ አይገባም
ከሕገወጥ ፍልሰት ጋር በተያያዘ የአውሮጳ ኅብረት የአስቸኳይ ጊዜ መተማመኛ ድጎማ (Emergency Trust Fund - ETF) በማለት ለኢትዮጵያ የመደበው ገንዘብ ወደ ህወሃት ኮሮጆ እንደማይገባ ተነገረ፡፡ በኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትን እንደምክንያት በማድረግ ድጎማው እንዲከለስ ወይም እንዲሰረዝ ዩሮአክቲቭ ያቀረበው ጥያቄ ለመረጃው ይፋ መሆን ምክንያት ሆኗል፡፡ አንድ ጊዜ በቃል በሌላ ጊዜ ደግሞ በኢሜይል ከኅብረቱ በኩል የተሰጠው መረጃ የኅብረቱን የድጎማ አከፋፈል በተመለከተ የጠራ አቋም የማያሳይ ድንግዝግዝ መረጃ ሆኗል፡፡ በህገወጥ መንገድ ከአፍሪካ የሚፈልሱት ዜጎች የአውሮጳውያን መንግሥታት ራስምታት ከሆኑ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፍልሰት መጠኑ መጨመሩና ከዚያ ጋር ተያይዞ የሚጠፋው የሰው ህይወት አውሮጳውያኑን በስፋት ያነታረከ ነው፡፡ … [Read more...] about የአውሮጳ ኅብረት ድጎማ ህወሃት ኮሮጆ አይገባም
CSOs: Addressing the escalating human rights crisis in Ethiopia
To Permanent Representatives of Members and Observer States of the UN Human Rights Council Geneva, 8 September 2016 RE: Addressing the escalating human rights crisis in Ethiopia Your Excellency, The undersigned civil society organisations write to draw your attention to grave violations of human rights in Ethiopia, including the recent crackdown on largely peaceful protests in the Oromia and Amhara regions. As the UN Human Rights Council prepares to convene for its 33rd … [Read more...] about CSOs: Addressing the escalating human rights crisis in Ethiopia
ቂሊንጦ – “የተረሸኑት” እነማን ናቸው?!
“ወይኔ ልጄ፣ እጅ እግሬ ልጄ፣ ወይኔ ልጄ፣ ወዴት ነህ ልጄ፣ የት ላግኝህ ልጄ? እምኑ ጋር ነህ? ልጄ … ልጄ … ልጄ … ልጄ …” ጥቁር ቦርሳቸውን በወገባቸው ተሸክመው፣ ቂሊንጦ እስር ቤት ደጅ የሚያነቡ እናት ለቅሶ!! ሁሉም ያነባሉ። ሁሉም ያለቀሳሉ፣ የሚሰማ ግን የለም። እንደውም “ዘወር በሉ” እየተባሉ ይደገንባቸዋል። “ሊታረሙ በህግ ከለላ ስር ሆነዋል” የተባሉ ወገኖች “ተረሽነዋል” የሚለው አስተሳሰብ እየጠነከረ መጥቷል። ለቤተሰቦቻቸው እንደምን ተቆጥረው ይሁን? ይህ ሁሉ የጭካኔ ግፍ ወዴት ይመራን ይሆን? የብዙዎች ጥያቄና ስጋት ነው። በየሰዓቱ የሚወጡት መረጃዎች ደግሞ ስጋቱን የሚያግሉና ቁጣን የሚቀሰቅሱ ሆነዋል። የህወሃት ሹሞችም “የሆነው ነገር ሁሉ የተከሰተው በዕቅድ አይደለም” ይላሉ፡፡ በአልሞት ባይ ተጋዳነት የሚውተረተረው ህወሃት አሁንም አለሁ ቢልም የቂሊንጦ ጉዳይ … [Read more...] about ቂሊንጦ – “የተረሸኑት” እነማን ናቸው?!
በንጹሀን ዜጎች ላይ የሚፈጽመው ጭፍጨፋ ይቁም!!
የመግለጫውን ሙሉ ቃል ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ … [Read more...] about በንጹሀን ዜጎች ላይ የሚፈጽመው ጭፍጨፋ ይቁም!!
“የገደሉት ልጄ አስከሬን ላይ ቁጭ በይ ብለው ደበደቡኝ” ደምቢ ዶሎ የተገደለ ወጣት እናት
በቄለም ወለጋ ዞን ደምቢዶሎ ከተማ ውስጥ ትናንት ማክሰኞ ማምሻው ላይ ከመንግሥት ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። የአንደኛው ወጣት ወላጅ እናት እኔንም የልጄ አስከሬን ላይ ጥለው ደበደቡኝ ብለዋል። በመንግሥት ታጣቂ ጥይት ህይወታቸው ያለፈው ሁለቱ ሃይሉ ኤፍሬም እና ኢብሳ ሩንዴ የሚባሉ ሲሆኑ የ16 ዓመቱ ወጣት ሃይሉ ኤፍሬም ከተማዋ ውስጥ ተኩስ በመከፈቱ ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር ከተኩሱ ለማምለጥ ሲሮጥ መትተው ገደሉት ሲሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል። “ደሞቢ ዶሎ መሃል ከተማ ነበር ተኩስ የተጀመረው። ወደ ቀበሌ ዜሮ አምስት አካባቢም ተኩስ ነበር ። ልጆቹን እያባረሩዋቸው ሲመጡ ወጣት ሃይሉ ኤፍሬም በቅጽል ስሙ ቦጌ ነው የሚባለው ቀበሌ ዜሮ ሰባት በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ አቅራቢያ ነው የተገደለው” ብለዋል የአሜሪካ ድምፅ … [Read more...] about “የገደሉት ልጄ አስከሬን ላይ ቁጭ በይ ብለው ደበደቡኝ” ደምቢ ዶሎ የተገደለ ወጣት እናት
“የምትሰሙ ከሆነ ነጻ አወጣዋለሁ ለምትሉት ሕዝብ ይጠቅማል!”
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ የዛሬ ሁለት ዓመት መስከረም 14፤2007ዓም ለህወሃት ሊቀመንበር በግል እና ለህወሃት መሪዎች በጋራ እንዲሁም ለትግራይ ተወላጆች በወቅቱ ወደ ዕርቅ ሊያመጣ የሚችል ደብዳቤ ልከው ነበር፡፡ ይህንን መልዕክት ደግመን ልናትም ስናስብ ምላሽ አግኝተው እንደሆነ ለጠየቅናቸው "ለደብዳቤዬ ከህወሃት በኩል ምላሽ አላገኘሁም" በማለት ለጎልጉል ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ደብዳቤው ግልባጭ የተደረገላቸው መንግሥታት፤ ድርጅቶችና እንዲሁም ዓለም አቀፍ ሚዲያ መረጃውን መዝግበው ይዘውታል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ አቶ ኦባንግ "የዘር ማጥፋት አደጋው የተጠነሰሰው በራሳችሁ ነው፤ የምትሰሙ ከሆነ ነጻ አወጣዋለሁ ለምትሉት ሕዝብ ይጠቅማል!" በማለት የድርጅታቸውን (አኢጋን) አቋም በድጋሚ አሰምተዋል፡፡ ከጥቂት ቀናት በፊት ኦባንግ ከአብርሃ በላይ … [Read more...] about “የምትሰሙ ከሆነ ነጻ አወጣዋለሁ ለምትሉት ሕዝብ ይጠቅማል!”