ልጆች ሆነን ታላላቆቻችን ጉልበት አለን ብለው በደል ሲፈጽሙ "እግዚአብሔር በቀዳዳ ይየው!" እንል ነበር፤ ለመርገምም እየፈራን አንዲያው ድርጊቱ እንዲመዘገብልን ማሳሰባችን ይመስለኛል፤ አሁንም እንደዚያ ለማለት ይቃጣኛል፤ ግን አግዚአብሔር በሰማይ ላይ መኖሩን፣ በእያንዳንዳችን ውስጥ መኖሩን የቤተ ሃይማኖት ሰዎች እንኳን ማመናቸው በሚያጠራጥርበት ዘመን ለዓለማዊ ባለሥልጣኖች የእግዚአብሔርን ስም ማንሣት ፋይዳ ይኖረዋል ብዬ አልገምትም፤ ሆኖም እኔ ስለማምንበት የራሴን አሳውቃለሁ፤ ኢትዮጵያ የእግዚአብሔር አገር ነች፤ ኢትዮጵያን ጎድቶ የተጎዳ እንጂ የተጠቀመ የለም፤ ኢትዮጵያን አዳክሞ የደከመ እንጂ የበረታ የለም፤ ኢትዮጵያን አደህይቶ የደኸየ እንጂ የበለጸገ የለም፤ ኢትዮጵያን አዋርዶ የተዋረደ እንጂ የተከበረ የለም፤ ይህ የታሪክ ሐቅ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ባለሥልጣኖች ዓላማችሁ ምንድን ነው? … [Read more...] about ይድረስ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ጉልበት ላላችሁ ሁሉ
Archives for March 2016
ኢትዮጵያን የሚወክሉ የተለያዩ ወገኖች፤
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መግለጫ መጋቢት 1፤ 2008ዓም፤ ዋሽንግቶን ዲሲ፤ የአፈጻጸም ማጠቃለያ፤ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) የካቲት 6፤ 2008ዓም (February 14, 2016) በአሜሪካ የሜሪላንድ ጠቅላይ ግዛት ሲልቨር ስፕሪንግ ከተማ ባደረገው ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ “የኢትዮጵያ የዕርቅና ርትዓዊ ፍትሕ ምክርቤት” መመሥረቱን ይፋ አድርጓል፡፡ ምክርቤቱ የተመሠረተው ሕዝባዊ ጉባዔው ከመካሄዱ በፊት በነበሩት ሦስት ቀናት ውስጥ ኢትዮጵያን የሚወክሉ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ወገኖች ባካሄዱት ስትራቴጂካዊ ውይይት ነበር፡፡ ምክርቤቱ “የእኛ ለኛ” ወይም የሕዝብ ለሕዝብ ንቅናቄ ሲሆን ዕርቅ፣ የጉዳት ፈውስና ርትዓዊ ፍትሕ በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን መካከል ለማምጣት የሚተጋ ይሆናል፡፡ አጀማመር፤ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ገና … [Read more...] about ኢትዮጵያን የሚወክሉ የተለያዩ ወገኖች፤
በዐማራው ነገድ ላይ የደረሰ የዘር ማጥፋትና ማጽዳት ወንጀል ጥናት ውጤት ማጠቃለያ ዘገባ!
ኢትዮጵያ አገራችን እያከተመ ባለው ምዕተ-ዓመት ሁለት የተለያዩ የማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፓለቲካዊ ለውጦችን አስተናግዳለች። የመጀመሪያው በ1966 የፈነዳው አብዮትና ሶሻሊስታዊ እንቅስቃሴ ሲሆን፣ ሁለተኛው በክስተቱም ሆነ በውጤቱ እጅግ የተለየው ደግሞ ከ1983 ጀምሮ የተንሰራፋው የዘመነ መሳፍንት ተምሳሌት ወያኔ መራሹ ፓለቲካ ነው። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about በዐማራው ነገድ ላይ የደረሰ የዘር ማጥፋትና ማጽዳት ወንጀል ጥናት ውጤት ማጠቃለያ ዘገባ!
ኢህአዴግ እንዲህ ነው
ዛሬ በስልጣን ላይ ያለው ጉደኛ ቡድን ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ በየጊዜው ቅርጹንም ሆነ ይዘቱን ሲቀያይር መኖሩን መስራቾቹ ነግረውናል። አንዳንዱን እያየንም ታዝበናል። ከመገለጫዎቹ ጥቂቶቹ አንባገነንነት፣ ገዳይነት፣ አፋኝነትና ጠባብነት ወይም ዘረኝነት እንዲሁም ጥላቻ ናቸው። ከዚህ ጥቅል ተፈጥሮው ሌላ ስልጣን ከያዘም ጊዜ ጀምሮ የሚታዩበት ግልፅ ባህርያት አሉ። አንደኛው እውነታን መካድ ወይም አለመቀበል ነው። አይኑ ስር ያለውን ግልፅ እውነታ አይቀበለም። በተለይ ተቃውሞ ወይም ውድቀት ወይም የሃሳብ ልዩነት ከሆነ በጭራሽ አይደራደርም። አዘውትሮ የሚጠቀምበት አሰልች ስልት ለእውነታው ወይም ለችግሩ ሃሰተኛ ባለቤት መፈለግ ነው። ይህም ተቃዋሚ ፓርቲ፣ አክራሪ ቡድን፣ ፀረሰላም ሃይል፣ ፀረልማት፣ ወዘተ ሊሆን ይችላል። እንዴት ያለ በሽታ ነው ጃል! ትክክለኛውን ህመም ለይቶ ትክክለኛ … [Read more...] about ኢህአዴግ እንዲህ ነው
ኦህዴድ ሳያገግም፤ ብአዴን ሊደገም?
ኢትዮጵያን በተገንጣይ ስም የሚመራው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር - ህወሃት፣ የገጠመው ቀውስ እየተለጠጠበት ነው። ኦህዴድ አደረጃጀቱ ሊጠገን በማይችልበት ሁኔታ ተናግቶበታል። ይኽው ወረርሽኝ ወደ ሌሎች ገባር ድርጅቶች መስፋፋቱ የማይቀር ቢሆንም ብአዴን ውስጥ ቀውስ ስለመነሳቱ መረጃዎች ከቀድሞው በላይ ጎልተው እየወጡ ነው። በ1997 ምርጫ ኢህአዴግን ከውድቀት ጉድጓድ ያወጣው ኦህዴድ፣ ህወሃት በአንጃ ተቧድኖ ሲባላ የመለስን ወገኖች የታደገው ብአዴን አሁን ለህወሃት መከራ ሆነውበታል። አጋር የሚባሉት ድርጅቶችም ውስጥ ተመሳሳይ ችግሮች እንዳሉ የራሱ የህወሃት መገናኛዎች እየመሰከሩ ነው። የችግሩ አሳሳቢነት ቀላል ባለመሆኑ ኦሮሚያና ጋምቤላ ተሸንሽነው “በጊዚያዊ ወታደራዊ አስተዳደር” ሥር ወድቀዋል። ይህንኑ እውነት አሁንም የራሱ የህወሃት ልሳኖች አምነው ይፋ አድርገውታል። አንድ … [Read more...] about ኦህዴድ ሳያገግም፤ ብአዴን ሊደገም?
የመለስ ዜናዊ ራእይ
መለስ ዜናዊ ለኢትዮጵያ የጠላት ጠላት ደመኛ ጠላት ነው። ከአባቱ፣ ከእናቱና ከአያቶቹ የወረሰው በኢትዮጵያና በሕዝቧ ላይ የፈጸመው ግፍ፤ የሃገር ማፍረስ ድርጊት በታሪክ የማይረሳ ነው። እሱ ብቻ ሳይሆን የህወሓት አመራርንም ይጨምራል። የስም ዝርዝራቸውን በተለያዩት ጽሁፎቼና ከዚህ በላይም ስላካተትኳቸው እንሱን መመልከትና ማመሳከር ይቻላል። የመለስ ዜናዊ ራእይ በኢትዮጵያ ልማት፣ እድገት፣ ዲሞክራሲ ማለትስ ምን ማለት ነው? በእርሱ አመራር ለ21 ዓመታት ኢትዮጵያ በልማትና በዲሞክራሲ አብባለች የሚሉት የህወሓት ደጋፊዎችና አጋር ድርጅት ተብለው የሚጠሩት ጸረ-ሕዝብና ጸረ-ኢትዮጵያ ስብስብ ብቻ ናቸው። ብዙ ለሆዳቸው ያደሩም አሉባቸው። ነገሩ የተጋላቢጦሽ ነው። መለስ ዜናዊ የሚመራው ህወሓትና አመራሩ በተፈጥሮው ጸረ-ሕዝብና ጸረ-ዲሞክራሲ ነው። ህወሓት አፈጣጠሩ አምባገነን እና ፋሽስት፣ … [Read more...] about የመለስ ዜናዊ ራእይ
“የመሬት ባላባቱን” አባይ ማን ይድፈራቸው?
ከተለያዩ አቅጣጫዎች በተቃውሞና ዓመጽ የተወጠረው ህወሃት/ኢህአዴግ በአስሩም ክፍለከተሞች የሚገኙ እስከ 600 የሚደርሱ የመሬት ባለሙያዎችን ካገደ በኋላ የአዲስ አበባ የመሬት አስተዳደር ሞሳኞች ያላቸውን 85 አመራሮችና ሠራተኞችን በቁጥጥር ሥር አውሏል፡፡ “የመሬት ከበርቴውን” አባይ ጸሃዬንስ ማን ይደፍራቸው ይሆን የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል፡፡ በአባይ ጸሃዬ “ልክ እናስገባለን” ተግባራዊ እንዲሆን የታሰበው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በገጠመው ከፍተኛ ተቃውሞ ከተስተጓጎለ በኋላ ህወሃት/ኢህአዴግ ማስተር ፕላኑን “ትቼዋለሁ” ቢልም የኦሮሞ ሕዝብ ያስነሳው ተቃውሞ ግን እስካሁን አልበረደም፡፡ “መልካም አስተዳደርን አሰፍናለሁ” በሚል ኢህአዴግ የሕዝቡን ቀልብ ለመሳብ ከላይ ታች እየተራወጠ ነው የሚሉ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንደሚሉት ኪራይ ሰብሳቢነት ለመዋጋት በሚል … [Read more...] about “የመሬት ባላባቱን” አባይ ማን ይድፈራቸው?
ህወሃት ራሱን “ሳያጸዳ” በሌላው ዘምቷል
“የኢህአዴግን መርህ እስከተከተለ ድረስ መሃይምም ቢሆን ሚኒስትር እናደርጋለን” ያሉት መለስ ዙሪያቸውን “የበታች” በሆኑ ሹሞች አስከብበው የቆዩት ያለምክንያት አልነበረም፡፡ “አዋቂ፣ ጠቢብ፣ ባለራዕይ፣ ምንተስኖት፣ …” የሚሉ “ማዕረጎችን” አስገኝተውላቸዋል፡፡ ከዚህ አንጻር የፈለጉትን ሥልጣን ላይ ያስቀምጣሉ፤ ከዚያ በሙስና ያበሰብሳሉ፤ ከዚያም ወደ “ቆሻሻ ቅርጫት” ይጥላሉ፡፡ በሕይወት ለቆዩት “ቅርጫቱ” ትልቅ መድህን ሲሆን ለዚያ ያልታደሉት ግን ትርጉሙ ሌላ ነው፡፡ ይህ የመለስ አሠራር የህወሃት መመሪያ ሆኖ ቆይቷል፤ አሁንም እየተሰራበት ነው፡፡ በኦሮሞ ከተሞች በተነሳው ሕዝባዊ ንቅናቄ የተደናገጠው ህወሃት ከረፈደ “ጽዳት” ጀምሯል፡፡ የችግሩ መንስዔ ራሱ ሆኖ “ልክ መግባት” ሲገባው ለህዝብ “ሥራ ላይ ነን” ለማለት “የኦህዴድን አመራሮች” ማንሳቱ አስታውቋል፡፡ የጎልጉል እማኝ … [Read more...] about ህወሃት ራሱን “ሳያጸዳ” በሌላው ዘምቷል
የጃዋር መሃመድ ቅኝቶች
መገናኛ ብዙሃንን መቼ እና እንዴት መጠቀም እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል። የሚፈልገውን ነገር ሁሉ ከፈጸመ በኋላ ግን እንደ በረሃ ተኩላ እያደፈጠ ይናከሳል። ሲናከስ ደግሞ ማንንም አይምርም። ውለታ የሚባል ነገር አያውቅም። ይሉኝታ አይነካካውም። እፍረትም በእርሱ ዘንድ የለችም። ከቶውን መቀበል እንጂ መስጠትን አያውቅም። አስር ተቀብሎ በዜሮ የሚሸኝ ጀግና ነው። በዚህ ተግባሩ አድናቂው ነኝ። “እኔ-ነኝ” ያለ የዲሲ ፖለቲከኛን ሳይቀር ከአንዴም ሁለቴ እንደማስቲካ እያኘከ መትፋቱን እንመሰክራለን። የጡት አባቱ የሆነው ኦነግንም ቢሆን "A Critical Assessment of the Oromo Liberation Front” በሚለው መጣጥፉ እንዳይሆን እንዳይሆን አድርጎ የጠረበ ፍጡር ነው። ይህ ሰው እንደገና ተመልሶ የ”ነፍጠኛውን ሚድያ” ለመጠቀም የማይሞክርበት ምክንያትም የለም። ጃዋር … [Read more...] about የጃዋር መሃመድ ቅኝቶች
ያገር ያለህ!!! የዳኛ ያለህ!!!
1/ መግቢያ በድሮ ጊዜ ሰው በሰው ሲበደልና ፍትሕ ሲጓደል ‘ያገር ያለህ’ ወይም ‘የዳኛ ያለህ’ በማለት ይጮህ ነበር፤ ይህ ዓይነቱ የተበዳይ ጮኸትም ለትውልድ መርገም እንዳይሆን ተብሎ በአካባቢው በሚኖሩ እድሜና ልምድ ጠገብ ሺማግሌዎች ገላጋይነት/ዳኝነት የበደለ እንዲክስ የተበደለ ደግሞ እንዲካስ በማድረግ ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ ይደረግ ነበር፤ እኔም ዛሬ በዲሞክራሲ ስም በምድራችን ውስጥ እየሆነ ያለውን አጠቃላይ እንቅስቃሴ /በተለይ ባለውለታ በሆነችው በኦርቶዶክስ ቤ/ክ ውስጥ/ ቀረብ ብየ ስመለከት ይህ እውነተኛ የፍትህ ፈላጊዎች ያገር ያለህ ጩኸት ትዝ ብሎኝ ለኢትዮጵያውን በሙሉ ለውይይትና ለመፍትሄው ፍለጋ ጭምር የሽማግሌ ዳኞች ያለህ በማለት ጮኸቴን ላቀርብ ተገደድኩ። መቸም ለተወሰኑ ዓመታት ከአገሩ ራቅ ብሎ ለኖረ ኢትዮጵያዊ የአዲስ አባባ ገጽታ ቀየር እንደምትልበት ይታመናል፤ … [Read more...] about ያገር ያለህ!!! የዳኛ ያለህ!!!