* ደርግ የረሸናቸው የንጉሡ ባለሥልጣናት 60 አይደርሱም ተብሏል * መፈንቅለ መንግሥቱ ቢሳካ ኖሮ ኤርትራ ከመገንጠል ትድን ነበር? * በዓሉ ግርማ መገደሉን ኮሎኔል ፍስሃ በመጽሐፋቸው ይፋ አድርገዋል በደርግ ዘመን በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ያገለገሉትና በመጨረሻም የአገሪቱ ምክትል ፕሬዚዳንት የነበሩት ሌተናል ኮሎኔል ፍስሀ ደስታ፤ከ20 ዓመት እስር በኋላ የፃፉት “አብዮቱና ትዝታዬ” የተሰኘ መፅሐፋቸው፤ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በሂልተን ሆቴል ሲመረቅ አብዛኛውን ታዳሚ ለክርክር ጋብዟል፡፡ ደግነቱ የውይይት መድረክ ተዘጋጅቶ ነበር፡፡ በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ ከታደሙት አብዛኞቹ የ1960ዎቹ ትውልድ አባላት ነበሩ፡፡ የደርግ ባለሥልጣናት፣ ከፍተኛ የጦር አዛዦች እንዲሁም ከደርግ በተቃራኒ ቆመው ሲፋለሙ የነበሩ የኢህአፓ፣ መኢሶንና ሌሎች በወቅቱ የነበሩ የፖለቲካ ድርጅቶች … [Read more...] about “አብዮቱና ትዝታዬ” ሲያከራክር ዋለ
Archives for November 2015
አንድ:- ከመጠምጠም መማር ይቅደም
በፌስቡክ የምንሰባሰበው ለመወያየት፣ አንዱ ከሌላው እንዲማር፣ መረጃዎችን በነጻነት እንድንለዋወጥ፣ ይህንን ሁሉ በማድረግ ራሳችንን ለማሻሻል፣ የእኛ መሻሻል እየተራባና እየተባዛ የአገርና የሕዝብ መሻሻል እንዲሆን፣ ከተቻለንም ከአገራችንና ከሕዝባችን አልፈን የምንታይ የዓለም አካል እንድንሆን መስሎኝ ነበር፡፡ ሳየው በዚያ መንገድ ላይ ያለንና ፌስቡክን ለበጎ ዓላማ እየተጠቀምንበት ያለን አይመስለኝም፤ ስለዚህ ወይ መታረም፣ አለዚያም በፌስቡክ ጊዜ ማጥፋቱን መተው ምርጫ ሊሆንብን ነው፡፡ ምናልባት 99.99% በእኔ ሰፈር ያሉ የፌስቡክ ተሳታፊዎች ወደፌስቡክ የሚገቡት ለመናገር ነው፤ መናገር የህልውናቸው ምስክር ወይም ማረጋገጫ አድርገው የሚወስዱት ጥቂት አይደሉም፤ ካልተናገሩ የሌሉ ይመስላቸዋል፤ ዋናው ነገር መናገር ይሆንና የሚናገሩት ነገር ወይም ጉዳይ ሌላው ቀድሞ ከተናገረው ጋር የሚያያዝ … [Read more...] about አንድ:- ከመጠምጠም መማር ይቅደም
ችጋርና የእውቀት ችጋር
በፈረንጆች ባህል እውቀት ሥልጣን ነው፤ እንዲያውም እውቀት ኃይል ነው ይላሉ፡፡ በኢትዮጵያ ባህል እውቀት ሥልጣን የለውም፤ እንዲያውም ሥልጣን እውቀት ይመስለናል፡፡ በ1951 ዓ.ም. በትግራይ ችጋርን በዓይኔ አይቻለሁ፤ በጆሮዬ ሰምቻለሁ፤ በአካሌ ቀምሼዋለሁ፤ ጠኔ ይዞኝ ተደግፌ ወደቤቴ ገብቻለሁ፡፡ በመቀሌ ያየኋት አንዲት የመቀሌ ወጣት እናት ከነሕጻንዋ በአእምሮዬ ተቀርጸውና ተቆራኝተውኝ በሕልሜም በእውኔም እየወተወቱኝ ስለችጋር እንዳጠና አስገደዱኝ፡፡ ችጋርን እያገላበጥሁ ከሰባት ዓመታት በላይ አጠናሁ፤ የጥናቴ ውጤት RURAL VULNERABILITY TO FAMINE IN ETHIOPIA: 1958-1977 በሚል ርእስ በህንድ አገር፣ በኒው ዴልሂ ከተማ ታትሞ በ1977 ዓ.ም. (በአአ በ1984) ወጣ፤ በአሜሪካ የተማርሁበት ክላርክ ዩኒቨርሲቲ ለጥናቱ ድጎማ የሚሆን የ$30,000 ለቀዳማዊ … [Read more...] about ችጋርና የእውቀት ችጋር
በደልን መላመድ ባርነት ነው!
የማሰብ ነፃነት ማጣት ባርያነት ነው፤ ያሰቡትን አለመናገር: ባርያነት ነው፤ ያሰቡትን አለመጻፍ: ባርያነት ነው፤ ፍትህ ማጣት: ባርያነት ነው፤ ከገዛ አገሩ መሰድደ: ባርያነት ነው፤ ተማሪው "መሬት ለአራሹ" ብል በደሙ የዋጀውን የመሬት ባለቤትነት መብት: ከገበሬው ነጥቆ በማፈናቀል: በድንበር ዘለል ከበርቴ መቸብቸብ፤ የባርያነት ቀንበርን መልሶ መጫን ነው፤ ሠራተኛውን በዓለም አቀፍ ዘራፊ ኢንደስትሪዎች፤ በገዛ አገሩ ጉልበቱን ማስበዝበዝ: ባርያነትን ማስፈን ነው፤ ምሁራንን በአገራቸው ጉዳይ ተሳትፎ እንዳይኖራቸው በየምክንያቱ ማግለል: ባርነትን እንዲነግሥ ማድረግ ነው፤ ወጣቱን ለሥራ አጥነትና ለስደት መዳረግ አገርን መግደል ነው፤ ዝምታ ባርነትን አሜን ብሎ መቀበል ነው፤ አድር ባይነት: ባርያ መሆን ነው፤ ሕዝብን በገዛ አገሩ የበይ ተመልካች እንዲሆን ማድረግ: የባርነት ሥርአትን ማስፈን … [Read more...] about በደልን መላመድ ባርነት ነው!
Enough has not been said about the hyenas
I recently published an article on this blog titled ”me, my country and corruption”. Its about corruption. Where by I have tried to discuss the rampant corruption by the Ethiopian dictatorial regime. The article articulated the issue from different perspectives. Aiming to give a general frame work how systematically complicated its together with remedies. For any one reading this, I kindly request you to read my previous article to have the full grasp. Here is the link-Habtamu Bogale’s blog. I … [Read more...] about Enough has not been said about the hyenas
ገሃዱ አሰቃቂ ረሃብ እና የማወናበጃው “የልማት ዕድገት” በኢትዮጵያ
በያዝነው ዓመት በአገራችን በኢትዮጵያ አስከፊ የርሃብ አደጋ እንደተስፋፋ ከተለያዩ የዜና አውታሮች ይደመጣል። በተቃራኒው ደግሞ የትግሬ-ወያኔ የሚቆጣጠራቸው የመገናኛ ብዙሃን በአገዛዙ ጥረት ስለተገኘው የልማት ትሩፋት ይለፍፋሉ። በአንድ አገር በአንድ ጊዜ ሁለት እጅግ ተቃራኒ ሁኔታን የሚያንጸባርቁ ዜናዎች ሲደመጡ እውነቱን አንጥሮ ማሣዬት ተገቢ ነው። ስለሆነም በዚህ መግለጫ ዕውነቱ የትኛው እንደሆነ ብቻ ሣይሆን የመፍትሔ ኃሣቦችንም ለማመልከት ተሞክሯል። በአገራችን በኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ጊዜያት ከፍተኛ የርሃብ አደጋዎች ተከስተዋል። በዚሁ ሳቢያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን አልቀዋል፤ አሁንም እያለቁ ነው። ለአብነት ያህል በንጉሡ ዘመን በ1958 ዓ.ም. እና በ1965-66 ዓ.ም. እንዲሁም በደርግ ጊዜ በ1977 ዓ.ም. የተከሰቱት የርሃብ አደጋዎች በአስከፊነታቸው እና በሕዝብ … [Read more...] about ገሃዱ አሰቃቂ ረሃብ እና የማወናበጃው “የልማት ዕድገት” በኢትዮጵያ
ፖሊስ የቤተሰብ አባላትን እየጠረነፈ ነው
ፖሊስ ቤተሰብን በወረዳ፣ በብሎክ ብሎም በቤት ደረጃ በማደራጀት እየጠረነፈ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልፀዋል፡፡ ከአሁን ቀደም በየካ ከፍለ ከተማ በየግቢው የታደሉ "የቤተሰብ ተጠሪ ፎረም" የሚሉ ቅፆችን በማስደገፍ መዘገባችን የሚታወቅ ሲሆን ሰሞኑን በሳሪስ በተመሳሳይ አደረጃጀት ቤተሰቦችን ለመጠርነፍ እየተሰራ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ቅፁ ላይ የቤተሰብ አባላት "በመኖሪያ ቤታችን ውስጥ የሚፈጠሩ ያለ መግባባቶችን በራሳችን ለመፍታትና ብሎም የአካባቢውን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ እንዲሁም ከፖሊስ ጎን ሆነን በማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት የድርሻችን ለመወጣት" በሚል ከቤተሰብ መካከል ለፖሊስ ተጠሪ እንዲወክሉ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህ የቤተሰቡ የፖሊስ ተወካይም ግቢው ውስጥ ተፈጠሩ የሚላቸውን ጉዳዮችና ሌሎችም መረጃዎች ለፖሊስ ማድረስ ይጠበቅበታል፡፡ ጥርነፋው ከቤተሰብ … [Read more...] about ፖሊስ የቤተሰብ አባላትን እየጠረነፈ ነው
በህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ባለሥልጣናት “ተዘርፈናል” – የሳውዲ ባለሃብቶች!
የሳውዲ ባለሃብቶች እነሱ “የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት” ያሏቸው አንዳንድ የህወሃት/ኢህአዴግ ሹሞች መሬታቸውንና መሣሪያዎቻቸውን የዘረፏቸው መሆኑን በማስታወቅ ክስ አሰሙ፡፡ ህዳር 15 ቀን 2008 ዓም በወጣው ታዋቂው የሳውዲ ጋዜጣ አረብ ኒውስ በኢትዮጵያ ባለው አገዛዝ አንዳንድ ባለሥልጣኖች መሬታቸውን እየተቀሙ በደልና ዘረፋ እየተፈጸመባቸው መሆኑን በአፍሪካ የሳውዲ ባለሃብቶችን ቡድን የሚመሩት ሞሀመድ አልሸህሪ የተባሉ ባለሃብት ለአረብ ኒውስ አስታውቀዋል። እኒሁ ባለሃብቶችን መርተው ወደ አፍሪካና ወደ ኢትዮጵያ ከአመታት በፊት ወደ የዘለቁት ባለሃብት አንዳንድ የአገዛዙ ኃላፊዎች በኢንቨስትመንት ፈቃድ ወደ ሀገሪቱ ያስገቡትን ንብረቶች ለመውረስ በእርሳቸውና በጓደኞቻቸው ላይ የወንጀል ክስ እንደተመሰረተባቸው ማስታወቃቸውን አረብ ኒውስ ዘግቧል። ቅሬታ አቅራቢው ሳውዲ ባለሃብት ሞሃመድ አልሸህሪ … [Read more...] about በህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ባለሥልጣናት “ተዘርፈናል” – የሳውዲ ባለሃብቶች!
ችጋር በሰው ዘር ላይ የሚፈጸም ወንጀል ነው
አለም እጅግ በሰለጠነበት በዚህ ክፍለ ዘመን፣ የሰው ልጅ በእውቀትና በቴክኖሎጂም በመጠቀበት ወቅት በሚሊዮኖች የሚገመቱሰዎች የሚላስ የሚቀመስ አጥተው፣ ሰማይና ምድሩ ተዳፍኖባቸው ከሞት አፋፍ የሚደርሱበትና ከፊሉም የሚሞቱበት አገርና ስፍራ ቢኖር እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ማሕበራዊ ፍትሕ የተጓደለባቸው፣ ሙሰኝነት መረን በለቀቀ መልኩ በተንሰራፋባቸው፣ ፍጹም የሆነ አንባገነናዊ ሰርዓት በሰፈነባቸው እና የህግ የበላይነት ባልተረጋገጠበት አገሮች ወይም እንደ ሶማሊያ ባሉ መንግስት አልባ ሆነው ለረዥም አመታት በትርምስና እልቂት ውስጥ በቆዩ ጥቂት አገሮች ብቻ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚከሰተውን ችጋር በተመለከተ እረዘም ላለ ጊዜ ጥናት ያካሄዱትን ፕ/ር መስፍን ወልደማሪያምን ጨምሮ በርካታ አለም አቀፍ ተመራማሪዎች በጥናቶቻቸው እንዳረጋገጡት የ‘ችጋር’ ምንጩ የተፈጥሮ አየር ንብረት መዛባት ወይም … [Read more...] about ችጋር በሰው ዘር ላይ የሚፈጸም ወንጀል ነው
History repeats itself after 30 years in Ethiopia
At present over 5 million people are affected by drought in the dictatorial Ethiopian regime (Ethiopian People's Revolutionary Democratic Front). The intensity of the drought is in many ways similar to the 1983's (during the rule of the Marxist Mengistu H/Mariam). Even though the cruelty of Mother Nature made millions in Ethiopia (especially in the Amhara region) starve to death, the incapable, ignorant and stubborn 25 years dictatorial rule worsen the problem. I remember the late prime … [Read more...] about History repeats itself after 30 years in Ethiopia