ዝናብ መች ይከፋል ቢዘንብ ምን አለ መብረቅ ባያስከትል እያጉረመረመ መዝነቡንስ ይዝነብ ማበስበሱን ቢተው ቀን የጣለ አይደል ሌት የሚያዳልጠው። ★★★ ሌቱን ሲዘንብ አድሮ ቀኑን ብራ ዋለ ለምን ይወቅሱታል ሰው መስራት ከቻለ ሲጥልም አይጣል ነው ዶፉ ከወረደ ማን አለብኝ ያለው ገደሉም ተናደ። ★★★ ዝናቡ ከመጣ "አህያ ማይችለው" በጊዜ 'ንጠለል ከወረደ አንዴ ነው እዲህ ከሚፎክር መጣሁ ቀረሁ እያለ ወርዶ ቢያሳርፈን እሱም እፎይ ባለ። ተጻፈ 8/5/2014 … [Read more...] about የዝናብ ሀሳቦች
Archives for October 2014
ለወገን ችግር ደራሹ ወገን ነው!
ባለፉት ፳፬(ሃያ አራት) ዓመታት በዐማራው ነገድ ተወላጆች ላይ የደረሰውን ግፍ እና በደል የቱን ያህል የከበደ እንደሆነ የሚያውቀው የግፉ እና የመከራው ተሸካሚ የሆነው ዐማራው መሆኑኑን ማንም አይስተውም። ያም ሆኖ ግን፣ ሰብአዊነት የሚሰማው ማናቸውም ሰው፣ በሰዎች ላይ የሚፈጸምን ግፍ እና በደል በራሱ ላይ እንደተፈጸመ በመቁጠር፣ ድርጊቱን ለማስቆም የሚችለውን ሁሉ ያደርጋል። ለተራቡት የርሃብ ማስታገሻ ያጎርሳል፤ ለታረዙት የእርቃን መሸፈኛ ከፈን ይለግሣል፤ ለተጠሙት የውኃ ጠብታ ያስጎነጫል፤ አልፎ ተርፎም ግፍ ፈጻሚዎች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ድምፁን ከፍ አድርጎ ይጮኻል። በዓለም ዙሪያ በስደት የሚኖረው ኢትዮጵያዊ በወገኖቹ ላይ የትግሬ-ወያኔ ዘረኛ አገዛዝ የሚፈጽመውን ግፍ ለዓለም ኅብረተሰብ ከማጋለጥ በተጨማሪ ምግብ፣ ልብስ እና መጠለያ ላጡ ወገኖቹ የሚችለውን ያህል እጁን ከመዘርጋት … [Read more...] about ለወገን ችግር ደራሹ ወገን ነው!
“ለእገሌ ሚ/ር እናገራለሁ፤ ለእገሌ ደኅንነት እደውላለሁ እያሉ አያስፈራሩን”
“አማካሪዎቼ ዓላማዬን የሚጋሩና የሚያስፈፅሙልኝ ሰዎች ናቸው፤” አቡነ ማትያስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ በፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ተጠርቶ የተካሔደው ስብሰባ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን ወቅታዊ ሁኔታ የማይገልጽ፣ መዋቅሩን ያልጠበቀ እና ጽ/ቤታቸው የማያውቀው መሆኑን በመግለጽ ተቃወሙ፡፡ “የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደራዊ አስተሳሰብ ማበልጸግ” በሚል ርእስ ከትላንት በስቲያ (መስከረም 29፤2007) በመንበረ ፓትርያርኩ አዳራሽ የግማሽ ቀን ስብሰባ በተደረገበት ወቅት፣ የፓትርያርክ አቡነ ማትያስን የመግቢያ ንግግር ተከትለው የተናገሩት ዋና ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ÷ “አሁን ወደ ስብሰባው ስገባ ነው መልእክቱን የሰማሁት፤ አጀንዳውም ከመቅረቡ በፊት ከቋሚ ሲኖዶሱ ወይም ከእኔ ጋራ ምክክር … [Read more...] about “ለእገሌ ሚ/ር እናገራለሁ፤ ለእገሌ ደኅንነት እደውላለሁ እያሉ አያስፈራሩን”
“መፈንቅለ ዓለም ባንክ!”
ካለፈው ሰኞ ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ያህል የዓለም ባንክ በተለይ ከሲቪል ማኅበረሰቦች ጋር ሲያካሂድ የነበረው ስብሰባ “በመፈንቅለ ዓለም ባንክ” ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያን በተለያዩ ዓለምአቀፋዊ መድረኮች በመወከል ድምጻቸውን የሚያሰሙት ኦባንግ “በመፈንቅሉ” ከተሳተፉት የዓለም ሲቪል ማኅበረሰቦች መካከል ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ነበሩ፡፡ የዓለም ባንክ ስለሚሰጠው ብድርና ዕርዳታ በተመለከተ ሊያካሂድ ያሰበው የፖሊሲ ለውጥ ሰነድ አፈትልኮ ከወጣ ጀምሮ በርካታ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚሟገቱ ዓለምአቀፍ የሲቪል ማኅበረሰቦችን ያስቆጣ ሆኗል፡፡ የፖሊሲ ለውጡ ግልጽነትና ተጠያቂነት በሌለው መልኩ ለታዳጊ አገራት ብድር ከመስጠት ባለፈ በተለይ አምባገነናዊ አገዛዝ በሰፈነባቸውና አገዛዞቹንም ለሚደግፉ ድርጅቶች ያለአንዳች ቅድመ ሁኔታ ገንዘብ መስጠትን የሚፈቅድ ነው፡፡ በዚህ አሠራር መሠረት ማንኛውም … [Read more...] about “መፈንቅለ ዓለም ባንክ!”
በግልጽ እንነጋገር
በአሁኑ ሰዓት በሀገራችን በኢትዮጵያ ያለውን ተጨባጭ የፖለቲካ ሁኔታ የማያውቅ ኢትዮጵያዊ የለም። ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ ሁላችንም አንድ ስምምነት ላይ ነን። በአንድነት ያልተገኘንበት፤ ምን ይደረግ? በሚለው መፍትሔ መሥጠቱ ላይ ነው። መፍትሔ ደግሞ ከመቅረቡ በፊት፤ ካለው ተጨባጭ ሁኔታ አልፎ፤ በግንዛቤያችን ደረጃ ያለንበትን መመርመሩ ግዴታ ይሆናል። እንግዲህ የዚህ ጽሑፍ ማጠንጠኛ ይኼው የግንዛቤያችን ጉዳይ ነው። በትግሉ ዙሪያ፤ ድርጅቶች፣ ምሁራን፣ ግለሰቦች ሞልተናል። እያንዳንዳችን የምንፈልገውን እናውቃለን። የሚያስማማን ደግሞ እያንዳንዳችን ከምንፈልገው መካከል ያለው የጋራ ፍላጎታችን ነው። ይህ የየግል ፍላጎታችን በሀገር ደረጃ ሲቀመጥና የጋራ የሆኑት ከመካከሉ ተጎልጉለው ሲወጡ፤ ሀገራዊ መታገያ ዕሴቶቻችን ነጥረው ብቅ ይላሉ። በዚህ ጽሑፍ፤ የሀገራችን፣ የትግላችን፣ የምሁራን ሚናና … [Read more...] about በግልጽ እንነጋገር
Obang addresses Civil Society Policy Forum at the IMF and World Bank meeting
Address by Obang Metho, Executive Director of the SMNE, to the Civil Society Policy Forum at 2014 Annual Meetings of the International Monetary Fund (IMF) and the World Bank Group (WBG), Washington, DC Thank you for inviting me to share in this panel discussion on “The Role of World Bank Indicators in Agricultural Development.” Today’s discussion is very relevant in that the World Bank is investing billions of dollars into agribusiness. Various new tools have been designed to measure and … [Read more...] about Obang addresses Civil Society Policy Forum at the IMF and World Bank meeting
“መጪው ምርጫ ይቅርብን”
ጥላ መጽሔት 11ኛ ዕትም “መጪው ምርጫ ይቅርብን” በሚል ርዕስ እና ከዚህ በታች ያሉትን ጦማሮችና ሌሎችን አካትታ ወጥታለች፡፡ ከቢን ላደን ግድያ በስተጀርባ ኢትዮጵያ በጋዜጠኞች በስደትም አንደኛ? የወያኔ ፍትሃዊ ምርጫ! መሬት ቆርሶ ... የአገር ስሜት ሳይኖረው ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡ የመጽሔቷን የሽፋን ገጽ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡ … [Read more...] about “መጪው ምርጫ ይቅርብን”
ዘዳግም!
የደመራ ዋና ዓላማ፤ “ሲቃወምና ሲጻረር የነበረውን የዕዳ ጽህፈት ክርስቶስ ከነ ሕግጋቱ በመደምሰስ በመሰቀል ላይ ቸንክሮ ከመንገድ አስወገደው” (ቆላ ፪፡፲፬)። ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው፤ የተደበቀውን እውነት ለመግለጥ፤ በሰው ላይ ተጭኖ የነበረውን ዕዳ ለመደምሰስ፤ ለሰባዊ ክብርና ልዕልና ተጻራሪ የሆነቱን ነገሮች ለማስወገድ ነው። [በሰፊው መረዳት ከፈለጉ ይህን ሰንሰለት ይጫኑ። ደመራ] ሙሴ አራቱን የኦሪት መጻሕፍት ከጻፈ በኋላ፤ በአራቱም መጻሕት የገለጻቸውን ጠቅለል አድርጎ በድጋሚ ያቀረበበት አምስተኛው መጽሐፍ ዘዳግም ይባላል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለሰባዊ ክብርና ልዕልና ተጻራሪ የሆነውን ለማስወገድ የገለጸባቸውን ኃይለ ቃላት ለማስጨበት “አማን አማን እብለክሙ” እያለ በመደጋጋም ተናግሯል። በጸሎተ ቅዳሴያችንም “ተንስኡ ለጸሎት” የሚለውን እንደጋግማለን። ቃጭልም … [Read more...] about ዘዳግም!
የኢትዮጵያ (የክርስቶስ) ቤተክርስቲያን የጣር ድምፅ!
ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኳቹህ እጽፍላቹህ ዘንድ ግድ ሆነብኝ ይሁ. 1፤3 በዚህ ጽሑፍ ላይ ጥንታዊቷና ሀገር በቀሏ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ያለችበትን ሁኔታ ከምእመናኗ ቁጥር በአስደንጋጭ ሁኔታ ማሽቆልቆል መንስኤውንና ተጓዳኝ ነገሮችን እናያለን፡፡ ይሄንን እንድናይ ግድ የሚልበትም ምክንያት ይህ አደጋ ኢትዮጵያዊ የሆነውን ማንነትና እሴት ለማጥፋት በተለያየ መንገድ ሲጥሩ የኖሩ ባዕዳን ጥረታቸው ሠምሮላቸው አሁን ላይ ኢትዮጵያዊነት በዜጎች ዘንድ ዋጋ እያጣና እየጠፋ ከመሄዱ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ስላለውና የሚነቃ ካለ ለማንቃት በማሰብ ነው፡፡ ስለ እውነት ለመናገር ከማንነት አንጻር ካየነው ለመረዳት ያለን አናሳ የታሪክ እውቀታችን ካልገታን በስተቀር ኢትዮጵያ ውስጥ ዛሬ ላይ በየትኛውም የእምነት ድርጅት ውስጥ ያለ ዜጋ ሁሉ ትናንትና የኢትዮጵያ … [Read more...] about የኢትዮጵያ (የክርስቶስ) ቤተክርስቲያን የጣር ድምፅ!
48 + 1 ደቂቃ ቢያልፍ ምን እንደሚከተል ግንዛቤ ነበር
ከስያሜው ጀምሮ እያነጋገረ ያለው የኢህአዴግ የአሜሪካ ጽ/ቤት የጥበቃ ሰራተኛ፣ በኢህአዴግ አባባል “ዲፕሎማት” አገር ለቆ እንዲወጣ ከተሰጠው የጊዜ ገደብ አንድ ደቂቃ ቢዘገይ ምን ሊከተል እንደሚችል አስቀድሞ ከስምምነት ላይ ተደርሶ እንደነበር ተጠቆመ። በስምምነቱ መሰረት ወዲ ወይኒ መባረሩ ከህወሃት ደጋፊዎችና አመራሮች ቅሬታ ማስነሳቱን አስመልክቶ አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ ዲፕሎማት “ወያኔዎቹ የተሰራላቸው ውለታ አልገባቸውም ማለት ነው” ሲሉ መደመጣቸውን የጎልጉል ታማኝ ምንጭ ተናገሩ። ለተቃውሞ ወደ ኢህአዴግ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ባመሩ ኢትዮጵያኖች ላይ ጥይት የተኮሰው የቀድሞው “ዲፕሎማት” ተመልሶ አሜሪካን መርገጥ እንዳይችል ተደርጎ የተባረረው በሁለቱም ወገኖች በተደረገ የውስጥ ስምምነት ነው። ለጉዳዩ እጅግ ቅርብ የሆኑ እንደገለጹት በአሜሪካው የምስጢር አገልግሎት (Secret … [Read more...] about 48 + 1 ደቂቃ ቢያልፍ ምን እንደሚከተል ግንዛቤ ነበር