የሃገራቸው ነገር ሲነሳ የሚከነክናቸው ወገኖቻችን ኢትዮጵያ ላለባት ችግር መፍት ሄው ምንድነው? እያሉ ኣጥብቀው ሲጠይቁ ይደመጣል። መፍትሄውም ብቻ ሳይሆን ችግሩ ማለትም እውነተኛው ችግር የት ላይ ነው ያለው? ብለውም ኣጥብቀው ሲደመሙ ይታያል። በዛሬዋ ኣጭር ጽህፌ በነዚህ መራራ ጥያቄዎች ዙሪያ ቁንጥል ኣሳብ ለማቀበል ኣስቢያለሁ። በርግጥም ሁላችን ኢትዮጵያዊያን የሆንን ችግሩ ምንድነው? ብለን ከጠየቅን ኣንዳንዶች ሊገረሙብን ይችላሉ። የችግሩ ተካፋይ ሆነን ሳለ፣ እየተጉላላን ያለነው እኛው ሆነን ሳለ፣ እንደገና መልሰን የሃገራችን ችግር የት ጋር ነው? ብለን ስንጠይቅ የምናወጋቸው ሰዎች ምናልባትም ግራ ሊጋቡ ቢችሉ ኣይደንቅም። ነገር ግን መጠየቃችን ትክክል ነው። በመጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ ትንቢተ ዳንዔል ላይ ኣንድ ናቡከደነጾር የተባለ ንጉስ ኣንድ ጊዜ ጠቢባንን ጠርቶ የህልም ፍቺ … [Read more...] about ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት ለችግሮቻችን የመፍትሄው ቁልፍ
Archives for March 2014
ኔልሰን ማንዴላና ህፀፆቹ
የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንትና የገዢው የኤኤንሲ /የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ/ፓርቲ ሊቀመንበር የነበሩትን ኔልሰን ሮሊህላህላ ማንዴላ ከሦስት ትውልድ ያላነሰ አፍሪካዊና የሌላው አህጉር ህዝብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል። እኝህ ሰው ይበልጥ ከሚታወቁባቸው ጉዳያቸው ውስጥ በአገሪቱ በነበረው አፓርታይድና ዘረኛ ስርዓት ለ27 ዓመታት መታሰራቸው ብሎም ከእስር በኋላ ለአሳሪዎቻቸውና በብዙ ሚሊዮን ጥቁር ደቡብ አፍሪካውያንን አንገብግበው ለገዙ የዘር መድሎ ለፈፀሙ እንዲሁም የግርፋት የግድያና የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎችን ለሰሩ ነጭ በዝባዦቻቸው ይቅር ማለታቸው ዋነኛው ነው። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ኔልሰን ማንዴላና ህፀፆቹ
“በዴሞክራሲ” ስም የሚደረግ የመሬት ነጠቃና የዘር ማጥፋት ወንጀል በኢትዮጵያ
በአይነቱ የመጀመርያ የሆነ የውይይት መድረክ የካቲት 27 2006ዓም/March 6, 2014/ በኦስሎ፣ ኖርዌይ ከተማ ተደረገ። Frontline Club Oslo በተባለ ድርጅት አማካኝነት በኢትዮጵያ በዴሞክራሲ ስም እየተካሄደ ያለውን የመሬት ነጠቃ እና የዘር ማጥፋት ወንጀል በተመለከተ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን አካላት በመጥራት ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል። በስብሰባውም ላይም ከውጭ ጉዳይና ከሌሎች መስሪያ ቤቶች፣ ከዩኒቨርሲቲ፣ ከመንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ በኦስሎ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ለጉዳዩ ቅርበት ያላችው አካላት ተገኝተዋል። ስብሰባውን የጠራው ድርጅት በመወከል ስብሰባውን በንግግር የከፈቱት ማርየስ ቮንዳርፈር እንደተናገሩት Fronline Club የተባለ ድርጅት በኦስሎ የተቋቋመው በያዝነው ዓመት ሲሆን አላማውም በዓለምአቀፍ ታዋቂ የፊልም እና የፎቶግራፍ ባለሙያዎችን፣ … [Read more...] about “በዴሞክራሲ” ስም የሚደረግ የመሬት ነጠቃና የዘር ማጥፋት ወንጀል በኢትዮጵያ
አያስቅም! አጭር ወግ
በብሄራዊ ትያትር አካባቢ አንዲት አነስተኛ ምግብ ቤት ነበረች። «ገሊላ ምግብ ቤት» ትባል ነበር። በአዲስ አበባ «ቁምራ» ከመግባቱ በፊት በአካባቢው ያሉ የመንግስት ሰራተኞች በምሳ ሰዓት ይህችን ምግብ ቤት ያጨናንቋት ነበር። ቁምራን የማታውቁ ካላችሁ፤ ለጽድቅ የሚደረግ መንፈሳዊ ጾም እንዳይመስላችሁ። እድገትና ትራንስፎርሜሽኑ ያመጣው አዲስ ክስተት ነው - ቁርስ ምሳና ራት በአንድ ጊዜ የመመገብ ዘዴ። «ኑሮ በዘዴ፣ ጾም በኩዳዴ» ይባል ነበር። ይህ አባባል አሁን መኖ በዘዴ በሚል ተቀይሯል። መቼም ሁሉም ነገር በነበር እየቀረ ነው። ጋዜጠኛ አቤል አለማየሁ በቅርቡ ባሳተመው "የአዲስ አበባ ጉዶች" የሚል መጽሃፉ ላይ ስለዚህች ታሪካዊ ምግብ ቤትም ትንሽ ብሏል። የምግብ ቤትዋ ባለቤት "ገሊላ ምግብ ቤት" የሚለው ጽሁፍ በከፊል አጥፍተውታል። አሁን ምግብ ቤት የሚለው ተነስቶ "ገሊላ" … [Read more...] about አያስቅም! አጭር ወግ
በአሁኑ ሰዓት ጦቢያን የሚመራት ማነው?
"በአሁኑ ሰዓት ጦቢያን የሚመራት ማነው “Who is in Charge?” የሚለው ጥያቄ ያሳሰባቸው ቧልተኞች የፈጠሩትን ቀልድ ላልሰማችሁ ላሰማችሁ፡፡ (ኮፒራይቱ የሰፊው ህዝብ እንደሆነ ይታወቅልኝ!) አንዱ ኤፍኤም ሬዲዮ ይደውላል - ዘፈን ለመምረጥ። ደዋይ - ዘፈን ለመምረጥ ነበረ፤ የእገሌን … ኤፍ ኤም- ማን እንበል? ከየት ነው? ደዋይ- የገዢው መደብ አባል ነኝ---- ከደቡብ! ኤፍ ኤም- (ደንገጥ ብሎ) ከደቡብ … እሺ ዘፈኑ ይቀጥላል … (የኤፍኤሙ ጋዜጠኛ ከድብልቅልቅ ስሜት ሳይወጣ ሌላ ዘፈን መራጭ ይደውላል) ኤፍ ኤም- ሄሎ … ማን እንበል? ከየት ነው? ደዋይ - ዘፈን ለመምረጥ ነበር ኤፍኤም- ራስህን አስተዋውቀን? ደዋይ - የገዢው መደብ አባል ነኝ - ከትግራይ! ኤፍኤም - እንዴትነው ነገሩ? አሁን ከደቡብ ደውሎ የገዢው መደብ አባል ነኝ … [Read more...] about በአሁኑ ሰዓት ጦቢያን የሚመራት ማነው?
“የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት ዘመቻ”
ይኽን ጽሑፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ ዐርብ የካቲት 28 ቀን (March 7, 2014) አንድነቶች “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባቤትነት” የሚል ህዝባዊ ንቅናቄ (ህዝባዊ ሰላማዊ ዘመቻ) በ14 ከተሞች {አዲስ አበባ፣ ደሴ፣ አዋሳ፣ አዳማ/ናዝሬት፣ መቀሌ፣ ደብረታቦር፣ ደብረ ማርቆስ፣ ድሬ ደዋ፣ ጅንካ፣ ቁጫ፣ አሶሳ፣ ነቀምት፣ ለገጣፎ፣ እና በተጓዳኝ ከተሞች ወልዲያ፣ ጋምቤላ፣ ም/አርማጨሆ(አብርሃ ጅራ)} እንደሚያደርጉ ማሳወቃቸው ነው። መግለጫቸውን እንዳነበብኩ ዘመቻው ለታሪካችን፣ ለተያያዝነው የነፃነት ትግል እና አይናችን ለተከልነበት የዴሞክራሲ ሽግግር የሚሰጣቸው ጠቀሚታዎች አሉን? የሚሉትን ጥያቄዎች አንስቼ ጥቂት ከራሴ ጋር ከተነጋገርኩ በኋላ ለዘመቻው ድጋፌን በመስጠት እና አንድነቶችን በማበረታት ተሳትፎዬን እንድገልጽ ህሊናዬ የግድ አለኝ። ስለዚህ የዚህ ጽሑፍ ግብ ዘመቻው … [Read more...] about “የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት ዘመቻ”
Sexual Violence and Rape against Ethiopian Women!
Sexual violence and rape are weapons used indiscriminately by TPLF/EPRDF cadres, soldiers and federal police in Ethiopia. They targeted innocent people living in villages and towns who are caught in the crossfire. Ethiopia is often described as being 'the most dangerous place in the world to be a woman'. The UN estimates that a staggering more than 200,000 women and girls have been victims of rape and/or sexual violence in Ethiopia during the last 15 years. The worst of the violence is … [Read more...] about Sexual Violence and Rape against Ethiopian Women!
ሰላማዊ ወይስ የትጥቅ ትግል ወይስ ማንፈራጠጥ
የተማረ ወይም የእውቀት ባለቤት እንደሆነ የሚነገርለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ክፍል ከወያኔ ጋር የሚደረገው ትግል ሰላማዊ ይሁን ወይስ በትጥቅ ትግል የሚለውን የጦፈ ክርክር ሲያደርግ ሃያ ሁለት ዓመታት ሆነው፤ ዳኛ የሌለበት ክርክር ስለሆነ የመደማመጥ ግዴታ ታይቶበት አይታወቅም፤ ስለዚህም በሁለቱ መሀከል ያለው ልዩነት ግልጽ ሆኖ አያውቅም፤ አንድ፣ ከሁሉ በፊት ሰላማዊ ትግል በሀሳብ ደረጃ መሆኑንና የትጥቅ ትግል ደግሞ በተግባር መሆኑን ለይቶ ለመረዳት ችግር ሆኖ ቆይቶኣል፤ በሌላ አነጋገር ሰላማዊ ትግል በሀሳብ፣ በንግግር፣ በተለያዩ ሀሳብን ለማስለወጥ መቀስቀሻ በሚሆኑ መንገዶች ተቃውሞን መግለጽ ነው፤ በአንጻሩ የትጥቅ ትግል በጠመንጃ ወይም በጉልበት ያለውን የአገዛዝ ሥርዓት ለመለወጥ የሚደረግ ሙከራ ነው፤ ሁለት፣ እንዲህ ከሆነ በሰላማዊ ትግል ለሚያምኑ ሰዎች ያለምንም ጥርጥር በተለያዩ … [Read more...] about ሰላማዊ ወይስ የትጥቅ ትግል ወይስ ማንፈራጠጥ
ኢህአዴግ – ሌባ ወይስ አገር አስተዳዳሪ?
ከላይ የጠየቅነው ጥያቄ ዛሬ የተነሳ አዲስ ነገር አይደለም። ኢህአዴግ መሰረቱን ዝርፊያ ላይ ያደረገ አገር አስተዳዳሪ መሆኑ ግብሩ ራሱ ምስክር ነውና "ሌባ አገር አስተዳዳሪ" ስለመሆኑ ማስተባበያ ሊያቀርብም አይቻለውም፤ አያስፈልገውም። ሌብነቱ አገርንና ህዝብን ወደ ገደል እየሰደደ መሆኑ ግን ሁሌም የሚያስጨንቅ ነውና ዛሬ እንደ አዲስ አነሳነው እንጂ!! ኢህአዴግ ግዙፍ፣ ሃብቱ በዶላር ካልሆነ በብር የማይቆጠር፣ በህገወጥ ንግድ ሰላማዊ ነጋዴዎችን የሚውጥ፣ ለብቻው መግቢያና መውጪያ የተዘጋጀለት፣ የተለየ ጨረታና የነጻ ቀረጥ እድል የሚበጅለት፣ በየትኛውም ተቋም እንደፈለገ መጋለብ የሚችል ልጓም አልባ የሆነ፣ በፈለገው ቦታና ማህበረሰብ ጥቅም ላይ እንዳሻው ከበሮ እየደለቀ የሚጨፍር፣ ጡሩምባ ይዞ የሚያንጠራባ፣ የፈለገውን ማስወገድ፣ ማሳገድ፣ ማስከፈት፣ ማዘጋት የሚችል፣ ድንበርና ኬላ … [Read more...] about ኢህአዴግ – ሌባ ወይስ አገር አስተዳዳሪ?
ጃፓን + ኢህአዴግ – ቻይና = መንበርከክ
ከቻይና ጋር የጀመሩት መወዳጀት ሥር ሰድዶ በሁለት እግሩ ከመቆሙ በፊት አቶ መለስ በሞት ከተለዩ በኋላ የኢህአዴግና የቻይና ግንኙነት በርካታ መንታ መንገዶች እየገጠሙት መጥተዋል፡፡ ከምዕራቡ ዓለም ከፍተኛ ገንዘብ በበጀት ድጎማም ሆነ በዕርዳታ የሚሠጠው ኢህአዴግ ምዕራባውያን ከቻይና ጋር ካላቸው ፍጥጫ አንጻር እየገባበት ያለው አጣብቂኝ በየጊዜው እየጨመረ መጥቷል፡፡ “ምርጫው በምርጫ” እየተወሳሰበበት የመጣው ኢህአዴግ በአንድ በኩል የአሜሪካንን ፍላጎትና ጥያቄ መፈጸምና ማስፈጸም፤ በሌላ በኩል ደግሞ አፈናውን ለማጠናከርና የግዛት ዘመኑን ለማርዘም ከቻይና የሚያገኘው በቅድመ ሁኔታ ያልታሰረ “ጥቅም” በሁለት ጽንፍ ወጥረውታል፡፡ አሁን ደግሞ ሌላ “ወጣሪ” ብቅ ብሎ በመንታው መንገድ ላይ ሌላ መንታ ፈጥሮበታል - ጃፓን! ቻይና በተለይ በአፍሪካ እያደረገች ያለችው የንግድ እንቅስቃሴና … [Read more...] about ጃፓን + ኢህአዴግ – ቻይና = መንበርከክ