የዘንደሮ ክረምት ከቀደምቶቹ በጥቂቱ ጠንከር ያለና ብዙዎችን በተለይም አዲስ አበቤዎችን እያማረረ ነው፡፡ ሌላው “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” የሚያስብለው ደግሞ የከተማዋ መንገዶች በአብዛኛው ጥገና ላይ መሆናቸውና በዚህም ሳቢያ የበርካቶች መኖርያና የንግድ ሱቆቻቸው መፍረሳቸው ነው፡፡ ይህንን ሁኔታ በምናብ ለማየት ለምትፈልጉ ቅዳሜ ነሀሴ 4 ቀን 2005ዓ.ም በወጣቺው ፋክት መጽሄት ላይ ፕ/ር መስፍን እንዲህ ሲሉ ገልጸዋታል “አዲስ አበባ በመሬት መናወጥ ፈራርሳ በመጠገን ላይ ያለች ከተማ ትመስል የለም እንዴ”:: ብቻ ክረምቱም ወደማለፉ እየተቃረበ አዲሱንም ዘመን ለመቀበል ሽርጉዱ ሳይጀመር አይቀርም፡፡ ምን ክረምቱ ብቻ ፖለቲካውም ክረምቱን ተከትሎ ከ8 ዓመታት በኋላ እሱም ጠንከር ያለ ይመስላል፡፡ ላለፉት ጥቂት ዓመታት በሀገር ውስጥ ሲደረጉ የነበሩት የፖለቲካ ፓርቲ እንቅስቃሴዎች … [Read more...] about ነሀሴ 26ን በደቦ ሸኝተን 2006 ዓ.ምን በተስፋ!
Archives for August 2013
የብዙኃኑ መገናኛዎች የያዙት አቋም ሕዝብና ሀገርን እንደሚጎዳ ሳያውቁ ቀርተው ወይስ?
ሰላም ጤና ይስጥልኝ አንባቢያን እንደምን አላችሁ? ይሄውላችሁ እንደምታውቁት ጥቂት ከማይባል ዓመታት ወዲህ ቀድሞ ከነበረን የሥነ-ኪናችን አትኩሮት በተለየ መልኩ አልፎ አልፎ ብቅ ከሚሉ አንዳንድ ዘፈኖች ወይም ሙዚቃዎች በስተቀር (በነገራችን ላይ ሙዚቃ የሚለው ቃል አማርኛ አይደለም፡፡ ሙዚክ ወይም ሚዩዚክ የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል በአገርኛ ለዛ ሲጠራ ነው፡፡ ልክ አፍሪካ አፍሪቃ፣ ስኩል አስኳላ እንደተባለው ማለት ነው፡፡) እናም ከጥቂት ዘፈኖች በስተቀር የዘፈኖቻችን በአንድ ነጠላ ርእሰ ጉዳይ ማለትም ጾታዊ ፍቅር ላይ እንዲያተኩሩ መደረጉ ሥነ-ኪን ወይም በዘልማድ ኪነጥበብ ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት ልታበረክተው የምትችለው የማይተካ ሚና ሀገራችን እንዳታገኝ መሆኗ እንደ ዜጋ አሳስቦኝና የድርሻየን ለመወጣት በዜጎች ሰብአዊ ልማት ላይ ያተኮረ “ፋሽን” የተሰኘ አንድ ዘፈን ዜማና … [Read more...] about የብዙኃኑ መገናኛዎች የያዙት አቋም ሕዝብና ሀገርን እንደሚጎዳ ሳያውቁ ቀርተው ወይስ?
ሞሄ አሳካህው! ዛሬም ዳግም ኮራን!
በሞስኮ 800 ሜትር ወርቅ ባለቤት በመሆን አገሩን ላኮራው መሃመድ አማን፤ ነቢዩ ሲራክ በዚህ ግጥም ኩራቱን ገልጾዋል፡፡ (ግጥሙን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ሞሄ አሳካህው! ዛሬም ዳግም ኮራን!
ሌሊሴ ተፈታች! ቀጥሎስ?
ላለፉት 5 ዓመታት ያህል ከልጆቿና ባለቤቷ ተለይታ በእስር ስትማቅቅ የነበረችው ሌሊሴ ወዳጆ መፈታቷ በርካታ ኢትዮጵያውያንን ማስደሰቱ ተጠቆመ፡፡ የጋዜጠኛ ሌሊሴን መፈታት አስመልክቶ Ayyaantuu News Online ለንባብ ባበቃው ዜና እንዳመለከተው በስደት አውስትራሊያ ከሚኖረው ከባለቤቷና ከልጆቿ ጋር ተቀላቅላለች፤ ድረገጹ ዜናውን በምስል በማስደገፍም አቅርቦታል፡፡ በጋዜጠኝነት ሲያገለግል የነበረው ባለቤቷ ዳቢሣ ዋቅጂራ አገር ጥሎ መሰደዱን ተከትሎ በማታውቀው ምክንያት የኦነግ አባል ነሽ በማለት ኢህአዴግ 10ዓመት ያለ አመክሮ ፈርዶ ወኽኒ እንዳወረዳት ይታወሳል፡፡ ይህንን ህዝብን ያበሳጨና ያስቆጣ ጉዳይ ሌሊሴ ከታሰረችበት ጊዜ ጀምሮ አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች መብት ጥበቃ ድርጅት (CPJ) ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን ሲያወግዙትና እንድትፈታ ሲሟገቱ መቆየታቸው … [Read more...] about ሌሊሴ ተፈታች! ቀጥሎስ?
በጥሩየ ዳግም ኮራን!
በዚህ ዓመቱ የዓለም አትሌቲክስ ውድድር በ10,000 ሜትር ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ወርቅ ያስገኘችውና በጃፓን በተደረገው የ1999ኙ የዓለም አትሌቲክስ የ10,000ሜትር ወርቅ ተሸላሚ ጥሩነሽ ዲባባ:: ትላንት የተደረገውን ውድድር ሲዘግቡ የነበሩት commentators የጥሩነሽን አንጸባራቂ ድል በሚከተለው ሁኔታ ገልጸውታል:: በመጨረሻው ዙር ተፎካካሪዎችዋን ጥሳ ስትወጣ:- "(Tirunesh Dibaba) the empress Ethiopian" ድል ከተቀዳጀች በኋላ፡- "Tirunesh Dibaba confirmed her status as one of the greatest female distant runners in history." ይህንን የጥሩነሽ ድል በአገራችን ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በማጣመር ነቢዩ ሲራክ “በጥሩየ ዳግም ኮራን” በማለት ይህንን ግጥም አቅርቧል፡፡ (ግጥሙን ለማንበብ እዚህ … [Read more...] about በጥሩየ ዳግም ኮራን!
ፖፕ ፓየስ 11ኛ አጼ ኃይለ ሥላሴን ለማስከዳት ስላደረጉት ሙከራ
እንደሚታወቀው፤ ኢጣልያኖች ኢትዮጵያን ለሁለተኛ ጊዜ በወረሩበት ዘመን፤ በዓለም-አቀፍ ሕግ በተከለከለ፤ በብዙ አውሮፕላኖች በተነሰነሰ የመርዝ ጋዝ በመጠቀም ጭምር፤ ለጊዜውም ቢሆን ወደ አዲስ አበባ ሲገሰግሱ፤ አጼ ኃይለ ሥላሴ ወደ እንግሊዝ ሐገር ተሰደው ለጥቂት ጊዜ እዚያ በመጠለል ትግላቸውን ቀጥለው ነበር። በዚያን ጊዜ፤ ሥልጣናቸውን ለኢጣልያን መንግሥት እንዲያስረክቡና በሚቸራቸው ገንዘብ የተንደላቀቀ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ ብዙ ጉትጎታ አጋጥሟቸው ነበር። በዚህ ጽሑፍ የሚተኮርበት ልዩ የነበረ ጉትጎታ፤ የቫቲካን፤ በተለይ በጊዜው የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን መሪ በነበሩት፤ የፖፕ ፓየስ 11ኛ ሙከራ ነው። ለዚህም ዋናው ማስረጃ፤ “Ethiopia Under Mussolini (Fascism and The Colonial Experience), 1985; በተሰኘው መጽሐፉ፤ አልቤርቶ ስባኪ (Alberto … [Read more...] about ፖፕ ፓየስ 11ኛ አጼ ኃይለ ሥላሴን ለማስከዳት ስላደረጉት ሙከራ
ጥላ መጽሔት
መጽሔቷ በዚህ ዕትም የሚከተሉትን ርዕሶችና ሌሎችንም ዳስሳለች፡፡ ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡ አባይ ሊያለማን ወይስ ሊያጠፋን ጨቋኙን ስርዓት በቃህ ልንለው ይገባል ስቃይና እንግልት ያልገታው ስደት ቀጥሏል ሰላም የወያኔ በደሎችና ህዝባዊ መፍትሔዎቹ የሙስሊሙ ኅብረተሰብ ስቃይ እና ሌሎችንም በርካታ ጽሁፎችን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡ … [Read more...] about ጥላ መጽሔት
SMNE Warning to the TPLF/EPRDF to Uphold Its Constitution:
Stop Unlawful Acts of TPLF/EPRDF –Sponsored Terrorism Against Ethiopian Muslims or Face Future Charges Ethiopians of Muslim faith have taken to the streets of Ethiopia to peacefully demand religious freedom in Ethiopia. According to their demonstration organizers, the numbers of protesters will increase to new levels of participation in the coming days and weeks; while at the same time, the TPLF/EPRDF government warns of new cracks down, some of which have already taken lives, injured young and … [Read more...] about SMNE Warning to the TPLF/EPRDF to Uphold Its Constitution:
እንዴት እንኑር!
… ለመሆኑ ከየት መጣን?…. ወዴት እንሄዳለን? …እንዴትስ እንኑር? የሚሉትን የፈላስፋውን ጥያቄ ስናነሳ፣ ግሪክ አገር አቴን ከተማ የዓለም ፈላስፋዎች ሰሞኑን ተሰብስበው “ስለ ዓለም ሁኔታ ይነጋገራሉ” ብለን አልገመትንም ነበር። እኛ በዚህ እትማችን ሰለ ዓለም ሳይሆን ስለ እኛው ስለ ራሳችን ችግር ነው አንዳንድ ነገሮቸን አንስተን ከግንዛቤ ውስጥ አስገብትን መለስ ብለን ለመመልከት የተነሳነው። “…እንዴት እንኑር? ” የሚለው ጥያቄ ሲሰነዘር የሚያስቆጣቸው ሰዎች እንደሌሉ ተስፋ እናደርጋለን። አንደንድ ጊዜ ከረጅም መላ-ምትና ግራ ከሚያጋቡ ጠማማ ጽንሰ-ሓሳቦች፣ ከቲዎሪ ዎች ይልቅ ቀላልና ጥሩ ጥያቄ ማቅረብ ፣ሌላውም ጎረቤት አገር ሆነ ራቅ ያሉ ሰዎች “እነሱስ እንዴት ይኖራሉ ?”ብሎ እራስን መጠየቅ ከብዙ ድካምና መነከራተት ያድናል። ግን ደግሞ ወደፊት ዘልቃችሁ እንደምታነቡት ፣ … [Read more...] about እንዴት እንኑር!
በውኑ መንፈስ ይታሰራልን?
እንደ ህወሃት አይነት አምባገነን መንግስታት ከተጠናወታቸው በርካታ ችግሮች መካከል ትግል እና ታጋይን ነጣጥሎ ያለማየት ችግር ሲሆን የትግል መሰረቱ ፍትህ እስከሆነ ድረስ፣የትግል መዳረሻው በተፈጥሮ የተገኘን መብት በችሮታ ካልሰጠናችሁ ከሚሉ አምባገነኖች መዳፍ ፈልቅቆ ለማውጣት እስከሆነ ድረስ በእርግጥም ይህ ትግል ከስጋና ከደም በላይ የተሻገረ በብዙሃን ላይ የሚሰርፅ መንፈስ ነው።ስለሆነም እንደመንፈስ የረቀቀው ትግል በታጋዩ ላይ ገዝፎ ይገለጥ ይሆናል እንጂ ታጋዩ ቢሰዋ አልያም በአምባገነኖች የግዞት እስር ቢወረወር ትግሉ አይታሰርም ደግሞም አይሞትም። ለምሳሌ ፀረ-አፓርታይድ ትግል ማጠንጠኛው ማህበራዊ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ፍትህን መሻት እንዲሁም የዘረኝነትን ክፉ ቀንበር መሰባበር ነበር። ነገር ግን በወቅቱ የነበሩ የዘረኛው አፓርታይዳዊ አገዛዝ አመራሮች የትግሉን ረቂቅ ወጣቶችንና … [Read more...] about በውኑ መንፈስ ይታሰራልን?