Dear Editors, I just read your report on would be "failed states" in 2030 at your site, which includes Ethiopia! This report is long due and there is at the moment no reason why this would not come true, unfortunately. It is alarming (actually all developments in the past century indicate towards that, high time we get the shoking awareness ) and something which we Ethiopians have to contain with all our energy, intelligence and commitment. Please see a paper attached here on the … [Read more...] about “Human – Ethiopia – Life” ሰው ፥ ኢትዮጵያ ፥ ሕይወት
Archives for January 2013
አሜሪካ በአፍሪካ ወታደራዊ የበላይነቷን ልታረጋግጥ ነው!
አዲስ በተያዘው የአውጳውያን ዓመት አሜሪካ በአፍሪካ ከፍተኛ ወታደራዊ የበላይነትን ሊያረጋግጥላት የሚችል ፕሮግራም ነድፋለች፡፡ ከሦስት ሳምንታት በፊት ይፋ የሆነውን ፕሮግራም ተግባራዊ ለማድረግ በሚያስችል ሁኔታ ላይ የተነደፈውን ዕቅድ የሚያስፈጽሙ 35 የአፍሪካ አገሮችም ተመርጠዋል፡፡ ምንም እንኳን ዜናው ይፋ ከሆነ የቆየ ቢሆንም የአሜሪካንን የመከላከያ ሚኒስቴር (ፔንታጎን) እንዲመሩ የታሰቡት ሪፓብሊካኑ ቸክ ሔግል ቀዳሚ ተወዳዳሪ መሆናቸው እስከሚገለጽ ድረስ የብዙዎችን ቀልብ አልሳበም ነበር፡፡ የአሜሪካንን ጦር ሠራዊት በየአገሩ በማዝመት ጉዳይ ላይ ጽኑ የተቃውሞ አስተሳሰብ የሚከተሉት ሔግል እንዲህ ዓይነቱን ፕሮግራም ለማስፈጸም ገጣሚ ሚኒስትር እንደሚሆኑ በሰፊው እየተነገረ ነው፡፡ የመከላከያ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ይፋ እንዳደረገው በአፍሪካ በየጊዜው እያገረሸ የሄደውን የአሸባሪዎች … [Read more...] about አሜሪካ በአፍሪካ ወታደራዊ የበላይነቷን ልታረጋግጥ ነው!
የጣመ ውይይት
ከዝግጅት ክፍሉ፤ አቶ ጋሻው ዓለሙ ጀምረውት አቶ አንዱ አለም ተፈራ የቀጠሉትና በማስከተልም አቶ ጋሻው ምላሽ የሰጡበት ውይይት እዚህ ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ አቶ ጋሻው ለሰጡት ምላሽ አቶ አንዱ አለም አጸፋውን በሚከተለው መንገድ አቅርበዋል፡፡ በዚህ ጽሁፍ ላይ አቶ አንዱ አለም እንደጠቀሱት እኛም አዘጋጆቹ ይህ ውይይት አገራዊ እንደመሆኑ ሌሎቻችሁም የምትሉት ቢኖር የበለጠ ውይይቱ ያዳብረዋል፤ ያሰፋዋል እንዲሁም ፖለቲከኞቻችን ትምህርት ሊወስዱ የሚችሉበትን ሃሳብ ሊያገኙበት ይሆናል፡፡ የበርካታዎች መሳተፍ ጥቅሙ ተዘርዝሮ የሚያልቅ ባለመሆኑ ሌሎቻችሁም በዚህ ጉዳይ ላይ ያላችሁን ሃሳብ፤ አስተያየት፤ ድጋፍ እንዲሁም ተቃውሞ በሠለጠነ መልኩ በማቅረብ ውይይቱን እንድታሰፉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ ለአቶ ጋሻውና ለአቶ አንዱ አለም እጅግ የከበረ ምስጋናችን ይድረሳቸው፡፡ የተቃዋሚ ፖለቲካ … [Read more...] about የጣመ ውይይት
“በ2030 ከሚከሽፉ መንግሥታት አንዷ ኢትዮጵያ ነች”
የአሜሪካ የብሔራዊ የደኅንነት ምክርቤት እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር በ2030 የሚከሽፉ 15 መንግሥታትን (failed states) ዝርዝር አውጥቷል፡፡ “በግጭት መብዛትና በአካባቢ ጥበቃ ቀውስ ምክንያት” ይከሽፋሉ ተብለው ከተተነበዩት የአፍሪካ፣ የእስያና የመካከለኛው ምስራቅ አገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ነች፡፡ እጅግ የነጠረ፣ ያልተዛባና የተጠና ዘገባ ለአሜሪካ የስለላ ተቋማት፣ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አውጪዎችና ለዓለምዓቀፍ ግንኙነት ተመራማሪዎች በማውጣት የታወቀው የአሜሪካ ብሔራዊ የደኅንነት ምክርቤት ከተቋቋመ በርካታ ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ ምክርቤቱ በሚያወጣቸው ዘገባዎች የአሜሪካ መንግሥትም ሆነ የተለያዩ መ/ቤቶች ተጽዕኖ እንደማያደርጉበት የሚናገር ሲሆን፤ ዘገባዎቹንም ከአድልዎ እና ከአሜሪካ መንግሥት አቋም ነጻ በመሆን እንደሚያዘጋጃቸው ይናገራል፡፡ የም/ቤቱ ዘገባ በተለይ ምርጫ … [Read more...] about “በ2030 ከሚከሽፉ መንግሥታት አንዷ ኢትዮጵያ ነች”
ትግሉ ይቀጥላል!!
ጥያቄዎቻችን በጆሮ ዳባ ልበስ ሊታለፉ አይገባም፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድና ገዢው ፓርቲ ተገደው እንዲሰሙ የማድረግ ህዝባዊ ትግል ይቀጥላል!! ከ33ቱ የፔቲሽን ፈራሚ ፓርቲዎች ባቀረብነው ጥያቄ ዙሪያ በቀጣይ የጋራ አቋም ላይ የተሰጠ መግለጫ 1. መግቢያ በአዳማ ከተማ በ2005 ምርጫ የጊዜ ሠሌዳ ላይ ለማወያየት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰበሰበን ወቅት ከተሣታፊ 66 ፓርቲዎች 41ዱ ከጊዜ ሠሌዳው በፊት የውድድር ሜዳውን መስተካከል በሚመለከቱ አበይት የምርጫ ጉዳዮች ልንወያይ ይገባል ከሚለው ኃሣብ በመነሣት እና በጉዳዩ ለመግፋት ፔቲሽን ፈረምን፡፡ በመቀጠልም በ29/02/05 ዓ.ም 18 ጥያቄዎችን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ /ኢብምቦ/፣ 13 ጥያቄዎችን ደግሞ በ08/04/05 ለክቡር ጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት፣ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈጉባኤ ጽ/ቤት አቅርበን ከቦርዱ … [Read more...] about ትግሉ ይቀጥላል!!
በደሴ የዳቦ ግራም የቀነሱ ሶስት ዓመት ተፈረደባቸው
በደሴ ከተማ ግብር ከፋዩ ነጋዴና ግብር ሰብሳቢው ክፍል አልተስማሙም። የከተማዋ ሹመኞች፣ ነጋዴዎች፣ በአነስተኛና ጥቃቅን ንግድ የታቀፉና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከንቲባውን ሲወቅሱ ተሰማ። በፓርላማ የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁሟል። በግምገማው ማብቂያ ከንቲባው ለፓርላማ አባላቱ ቢሯቸው ክፍት አድርገው እሳቸው ግን አልነበሩም። የጎልጉል ምንጮች እንደሚሉት ግምገማውን ተከትሎ የሚወሰድ ርምጃ ይኖራል። የዳቦ ግራም ቀንሰው የተገኙ ሶስት ዓመት ተፈርዶባቸዋል። የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አየር ላይ ያዋለው ዜና በደሴ ከተማ ግምገማና የመስክ ምልከታ የተደረገበትን ዋና ምክንያት አልጠቆመም። በዘገባው እንደተጠቆመው የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባካሄደው የመስክ ምልከታ የከተማዋን ከንቲባ የሚያጋልጥ አቤቱታ ቀርቦላቸዋል። ከደሴ ምክር ቤት አባል አንዱ የሆኑት … [Read more...] about በደሴ የዳቦ ግራም የቀነሱ ሶስት ዓመት ተፈረደባቸው
ያብለጨለጨ ሁሉ ወርቅ አይደለም!!
የሁሉም አለቃና የበላይ የሆነውን ሕዝብ ማስደሰት ያኮራል። የሚመሩትን ሕዝብና አገር ከልብ አክብሮ መገኘት ደግሞ ከኩራትም በላይ ነው። ይህንን በኳስ ያበደ ህዝብ፣ አገሩን ከምንም በላይ የሚያፈቀር ህዝብ መወከል ደግሞ ከበጎ ታሪክነቱ በላይ ከሽልማትና ከውዳሴ በላይ ነውና የኢትዮጵያ ልጆች ኩራታችሁ ታላቅ ይሁን። መልካም ዕድል ለአምባሳደሮቻችን!! ኢትዮጵያዊነት እንዲህ የሚጣፍጥ፣ ማንም ሊወስደውና ሊበርዘው የማይችል ሃያል በረከት መሆኑን ምክንያት ሆነው ላሳዩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት ክብር ይሁን ለማለት እንወዳለን። መልካም እድል ለአምባሳደሮቻችን ስንል በቂ ምክንያት ስላለን በፍጹም ኩራት ነው። በእግር ኳስ ፍቅር ለሚቃጠለው የኢትዮጵያ ህዝብ የደስታ ቀን ላመጣችሁ ውድ የኢትዮጵያ ልጆች የምንመኘው መልካም ምኞት ካለፉት የሰላሳ አንድ ዓመታት ውድቀት ጋር የተቀበረውን የድል … [Read more...] about ያብለጨለጨ ሁሉ ወርቅ አይደለም!!
ከእሁድ እስከ እሁድ
የላሊበላ ቅርስ አደጋ ላይ ነው ታሪካዊና የኢትዮጵያ የጥንት የስልጣኔ አሻራ ምስክር የሆኑት ውድ የላሊበላ ውቅር አቢያተክርስቲያናትና ቅርሶች በመፈራረስ ላይ መሆናቸው በተደጋጋሚ መጠቀሱ ይታወቃል። መንግስትም በተደጋጋሚ ቅርሶቹን ለማደስ እንደሚሰራ ማስታወቁም አይዘነጋም። በሳምንቱ መጨረሻ በስፍራው የተገኙ የተወካዮች ምክር ቤት አባላት “ስጋት አለን። ቅርሶቹ በመፈራረስ ላይ ናቸው” ሲሉ በመንግስት ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በተደጋጋሚ የላሊበላ ውቅር አቢያተ ክርስቲያናትና ውድ ቅርሶች የመፍረስ አደጋ እንደከበባቸው ቢገለጽም ምላሽ አለማግኘቱ አነጋጋሪ ሆኗል። መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነና የመንግስት ቴሌቪዥን ይፋ እንዳደረገው ታሪካዊዎቹ የኢትዮጵያ ልዩ መገለጫዎች የሚፈለጉት ለቱሪዝም ገቢ ብቻ ነው። በዓመት እስከ 40 ሺህ የሚደርሱ ቱሪስቶች ይጎበኟቸዋል። ከመቶ ሃያ ሚሊዮን ብር በላይ … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
አዲስ አበባ ረክሳለች!
ትውልድ አምካኝ ቤቶችን፣ ትውልድ አምካኝ ደላሎችን፣ በህጻናት የወሲብ ንግድ ገንዘብ የሚሰበስቡትን፣ ማጥፋት ቀላል ነው። ግን ተጠቃሚዎቹ ህግ አስከባሪዎቹ፣ ህግ አወጪዎቹና ዋናዎቹ “የአገሪቱ ህዳሴ ባለቤቶች” የሚባሉት በመሆናቸው አይታሰብም። አንዳንድ ዝግ ቤቶች በሲቪል ጠባቂዎች የሚጠበቁ ናቸው። አንዳንዴ ቤተመንግስቱንና ሟቹን የቤተመንግስት ነዋሪ ይጠብቁ የነበሩት በፈረቃ ይታደሙባቸዋል። ሃኪሞች፣ የህግ ባለሙያዎች፣ አገር የሚመሩት፣ ህግ የሚያስከብሩት፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ አውራ ባለስልጣናት፣ ህዝብ ፊት ቀርበው በልማት ስም የሚምሉት ሃብታም ተብዬዎች፣ የፖሊስ የበላይ አመራሮች፣ የስለላ አውራ ሰዎች፣ አጫፋሪዎች፣ የአቻ ፓርቲ አመራሮችና መካከል ጥቂት የማይባሉ ከዳር እስከዳር መመሸጊያቸው ዝግ ቤቶች ናቸው። አንዳንዴም ከዝግ ቤቶች ፍራሽ ላይ ሆነው የፖለቲካ መመሪያ … [Read more...] about አዲስ አበባ ረክሳለች!
የተቃዋሚ ፖለቲካ ኃይሎች ተቋማዊ ድክመት ወይስ የራዕይና ስትራተጂ ልዩነት?
በቀዳሚው ጹሁፌ “የተቃዋሚ ፖለቲካ ኃይሎች በድረ-መለስ ኢትዮጵያ፣ አይዲዮሎጂካል እና ስትራተጂካዊ ሁኔታዎች” እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር በ05/01/2013 በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ላይ በወጣው ላይ ተመስርተው አቶ አንዱ አለም ተፈራ በፈረንጆቹ አቆጣጠር 10/01/2013 በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ላይ “የተቃዋሚ ፖለቲካ ኃይሎች የተግባር ድክመት ወይንስ የግብና የእቅድ ልዩነት” ብለው ባወጡት ጹሁፍ ላይ ገንቢና አስተማሪ ሃሳቦችን ስላቀረቡ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሰዎት እላለው:: የዚህ ጹሁፍ አላማ በዋናነት በመጀመሪያ ጹሁፌ ላይ ያቀረብኩትን ሃሳብ በበለጠ የሚያብራራ ሲሆን፣ በተጨማሪም በአቶ አንዱ አለም ከተነሱት ገንቢ ሃሳቦች መካከል በበለጠ መብራራት አለባቸው ብዬ ያሰብኳቸውን ጉዳዮች ለመዳሰስ ነው:: (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about የተቃዋሚ ፖለቲካ ኃይሎች ተቋማዊ ድክመት ወይስ የራዕይና ስትራተጂ ልዩነት?