ሙስና በኢትዮጵያ አሳሳቢ ደረጃ መድረሱን ኢህአዴግ አይክድም። ኢህአዴግ ባለስልጣኖቹ በሙስና ስለመዘፈቃቸው ማመኑን የገለጸው “የመንግስት ሌቦች አስቸገሩኝ” በሚል ነው። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ “በሙስና የተለከፉ ዋጋቸውን ያገኛሉ” ሲሉ ስልጣን በያዙ ማግስት መዛታቸውን የሚያስታውሱ በስተመጨረሻ “ኢህአዴግና ኢህአዴግ ተፈራርተዋል” የሚል ድምዳሜ ላይ ነው። “ትልቅ ጫካ ሰርታችሁ የኛንም የናንተንም ሌቦች መደበቅ በመቻላችሁ ሁሉንም መመንጠር ስላልቻልን እየተተራመስን ነው” በማለት ጣታቸውን ወደ ነጋዴው ህብረተሰብ በመቀሰር ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር በአገሪቱ ያለውን ሙስና አስከፊነት በገለጹበት መድረክ “ስልጣን የመክበሪያ ብቸኛው መንገድ በሆነበት አገር ዘላቂ ሰላም ይኖራል ማለት ዘበት ነው። በኪራይ ሰብሳቢነት እንደ መንግስትም፣ እንደ ባለሃብትም መቀጠል አንችልም። እንደ … [Read more...] about ኢህአዴግና ኢህአዴግ ተፈራርተዋል
Archives for December 2012
ኢትዮጵያዊያን አሜሪካዊያንና የ2012 ዓመተ ምህረቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ምርጫ
እንደማንኛውም የአሜሪካ ኅብረተሰብ ሁሉ፤ በኢትዮጵያዊ አሜሪካዊነታችን፤ ማንኛውንም ምርጫ ከራሳችን ጥቅም አንፃር መመልከቱ ለሕልውናችን አስፈላጊ ጉዳይ ነው። እናም የ2012 ዓመተ ምህረቱን የአሜሪካ ፕሬዘዳንት ምርጫ የምንመለከተው፤ ከዚህ ተነስተን ነው። እኛ ምን ሠራን? ምን ተጠቀምን? ምን ተጎዳን? ምን አገኘን? ምን ቀረብን? ምን ማድረግ ነበረብን? በመጨረሻ ደግሞ፤ ምን ትምህርት ወሰድን? ይህ ነው ለምርጫው ግምጋሜ ጠቅላላ ይዘቱ፤ ከኢትዮጵያዊ አሜሪካዊነታችን አንፃር ሲታይ። የባራክ ኦባማ ከጥቁር ዝርያ መሆኑ ወይንም የሚት ራምኒ ነጭ መሆን ቦታ አልነበረውም። የዴሞክራቲክ ፓርቲው ማቸነፍ ወይንም የሬፑብሊኩ ፓርቲ መቸነፍ፤ ለኛ ትርጉሙ በፓርቲነታቸው ሳይሆን፤ የኛን ጉዳይ በሚመለከት ባላቸው አቁዋም ነው። በአሜሪካን ፓርቲ ስሌት ደግሞ፤ የምንፈልገውን ለማግኘት፤ የሚተማመኑበት የአንድ … [Read more...] about ኢትዮጵያዊያን አሜሪካዊያንና የ2012 ዓመተ ምህረቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ምርጫ
ከእሁድ እስከ እሁድ
ኢህአዴግን በኃይል ለማስወገድ ጥሪ ቀረበ በኢትዮጵያ ያለውን አገዛዝ ለመጣል ይቻል ዘንድ ለቀድሞው ሰራዊት፣ አሁን በስራ ላይ ላሉት የመከላከያ አባላትና በአገር ውስጥና በውጪ ስደት ላይ ላሉ ዜጎች ሁሉ የትግል ጥሪ ቀረበ። “የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል” በሚል ስያሜ ጥሪውን ያስተላለፈው ክፍል ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ከሚመሩት ድርጅት ጋር ግንኙነት እንዳለው ለማጣራት ያደረገው ሙከራ እንዳልተሳካለት ኢሳት ዘወትር እሁድ በሚያቀርበው የሳምንቱ ዜናዎች ላይ አስታውቋል። ኢሳት በሰበር ዜና ያቀረበው ይህ ዜና ከዋናው የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጋር ግንኙነት እንዳለውና እንደሌለው ለማጣራት ያደረገው ሙከራ ለጊዜው ባይሳካለትም፣ በቅርቡ ግን መረጃዎችን በማሰባሰብ በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ የሚያቀርብ መረጃ ለመስጠት እንደሚተጋ አስታውቋል። በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያለ ህዝብ ይሁንታ ላለፉት ሃያ አንድ … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
ከሶሪያ መሪዎች ጋር የሚደረገው ንግግር ጊዜው አልፎበታል፤
የኮፊ አናን ተልዕኮ በሶሪያ ላለው ትርጉም ያለዉ ዉጤት ማስገኘቱ አያስተማምንም። ይህ፤ ግጭቱ በየትኛዉም መልኩ መመለስ የማይችልበት ጠርዝ ላይ በመድረሱ ብቻ ሣይሆን፤ ከጅምሩም ምናአልባት የሶሪያ ገዥዎች ከወዲሁም ቢሆን በሰላም ሽግግሩ እንዲከናወን ፈቃደኛ አይሆኑምና ነው። የበሺር አል አሳድ ገዢ ቡድን፤ ቅንጣት የለዉጥ ሙከራ ሳያደርግና ተቃዋሚዎችን ሳያግባባ፤ ለምን በኃይል እንቅስቃሴዉን ለማጥፋት የወሰነበትን፤ መረዳት ያስፈልጋል። ባለፈው ዓመት፤ የመካከለኛው ምሥራቅ አምባገነን ገዥዎችን፤ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች አናግተዋቸዋል። ሶስት ዓይነት ዉጤቶች ተከስተዋል። በቱኒሲያና በግብፅ፤ ያለ ብዙ ሕይወት ጥፋት ፈላጭ ቆራጮቻቸዉን አስወግደዋል። ዚን ኤል አቢዴን ቢን አሊ እና ሆዝኒ ሙባረክ፤ ያለ ሕዝባዊ የርስ በርስ ግጭት ከሥልጣናቸው ተባረዋል። በግብፅ፤ ሙባረክ የመጨቆኛ ክንዱ አድርጎ … [Read more...] about ከሶሪያ መሪዎች ጋር የሚደረገው ንግግር ጊዜው አልፎበታል፤
Leveling the playing field in Ethiopia
The press release was short and to the point. It was only six paragraphs long and was written in a matter of fact way. There were no trumpets blaring, no press conference with TV lights and no lavish dinner to commemorate the event. The announcement reminded me of the proverb ‘best things come in small packages.’ So it was without much fanfare I read the most important announcement on Abbay Media and Quatero. Tucked among the news was the announcement regarding the formation of Ginbot 7 Popular … [Read more...] about Leveling the playing field in Ethiopia
ከሶማሊያውያን የሚበልጡ ኢትዮጵያዊያን ተሰደዋል
የአራት ዓመት ማነጻጸሪያ የቀረበበትን የሪፖርቱ አንያንዳንዱ ክፍል ያስገርማል። የማነጻጸሪያው ማሳረጊያ አስደንጋጭ ነው። መረጃው በአሃዝ፣ በኩኔታ፣ በባህሪው ስደትን ይገልጻል። ትንታኔው በካርታ፣ በስደቱ መነሻና መድረሻ መካከል፣ እንዲሁም በስደት መዳረሻ ላይ የሚያጋጥመውን አፈና፣ ቶርቸር፣ አስገድዶ መደፈር፣ ስቃይ፣ የባህር ሲሳይ የሆኑ ወገኖችን ይጠቅሳል። በተለይ በምስራቅ አፍሪቃ በኤርትራ፣ በኢትዮጵያ በኬንያ፣ በጅቡቲ፣ በሶማሊያና፣ፑንት ላንድ፣ ሶማሊ ላንድ፣ ስደትና የስደትን አስከፊነት በሪፖርቱ ተዘርዝሯል። አገራችን ኢትዮጵያ በስደት የተለዩዋት ዜጎቿ ቁጥር አገር አልባ ከሆነችው ሶማሊያ የሚልቅበትን ሁኔታ ያመላክታል። የዓለም የስደተኞች ኮሚሽን ከፍተኛ ኮሚሽርን /UNHCR/ በመጥቀስ የኖቬምበር 2012 ሪፖርቱን ያቀረበው Regional Mixed Migration … [Read more...] about ከሶማሊያውያን የሚበልጡ ኢትዮጵያዊያን ተሰደዋል
እንዴት ሀገር (ህዝብ) ይጥፋ?
እንዴትሀገር (ህዝብ) ይጥፋ? ያለመተማመን ስለዘራን ዘር እንሰበስባለን የማያልቅ ‘መከር’። ‘’መግዛት’’ እውቀት ሆኖ፣ ገንዘብና ሀይል አቋራጭ ጎዳናው ‘መቦልተክ’ ሆኗል። ሃይማኖት ተንቃ ስትሆን መቀለጃ የእግዚአበሄርም ቃል ሆነ ምነገጃ። ሳይሰሩ ያገኙት ሀብት፣ ክብር - ዝና ያስከብር ጀመረ መናቁ ቀረና። ፈረሀ - እግዚአብሄር ከልባችን ወ’ቶ ህገ - አውሬ ይገዛናል ሰው-ከሰው አባልቶ። ለመሾም - መሸለም፣ መክዳት - መከዳዳት ምግባራችን ሆኗል ዋናው ሀይማኖት። እያለን የሌለን ስለሆን ተመፅዋች መጠሪያችን ሆነ እናንተ ለማኞች። እውነት ተገንዞ ስለተቀበረ ውሸት ገዥ ሆነና ሰው ለ’ሱው አደረ። ፍቅርና ሰላም ፈላጊ ስለአጡ ተባረው ሄደዋል በአገር እንዳይመጡ። በሌሎች ደም - እምባ፣ ንዋይ … [Read more...] about እንዴት ሀገር (ህዝብ) ይጥፋ?
በአሜሪካ የ፳፮ ሕፃናትና መምህራን ግድያና ግንዛቤዬ
የምኖረው አሜሪካ ነው። አርብ ዕለት በከነቲከት ስቴት፣ ኒውታውን በምትባል ከተማ፤ ሳንዲ ሁክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ፤ ፳ የስድስትና የሰባት ዓመት የአንደኛ ክፍል ተማሪ ሕፃናትና ስድስት መምህርቶቻቸው በትምህርት ቤታቸው ተገደሉ። የተገደሉት የእናቱን መሣሪያዎች አንግቶ፤ መጀመሪያ እናቱን ከተኛችበት ገድሎ፣ የትምህርት ቤቱን መጠበቂያ ጥሶ በገባ የሃያ ዓመት ጎረምሣ ደጋግሞ በረፈረፈባቸው ጥይቶች ነበር። አሜሪካ ከላይ እስከ ታች በዚህ ኢሰብዓዊ ተግባር ተርገበገበች። ከዩጋንዳ ለሐዘኑ መልዕክትና ማስታወሻ ተላከ። ከቦዝንያ፣ ከአውስትራሊያ፣ በጠቅላላው ከዓለም ዙሪያ የሀዘን መግለጫዎች ጎረፉ። የአሜሪካ ፕሬዚዳንት በቦታው በመገኘት የስነ ሥርዓቱ ተካፋይ ሆነው፤ የሀገሪቱን አጠቃላይ የሀዘን ትብብር ለሙታን ወላጆችና ለከተማው ነዋሪዎች አቀረቡ። እኔም የዚሁ ሀገር ነዋሪ ሆኜ ጉዳዩን … [Read more...] about በአሜሪካ የ፳፮ ሕፃናትና መምህራን ግድያና ግንዛቤዬ
ኢትዮጵያ በጅቡቲ ወደብ መገንባት ጀመረች
በጅቡቲ አዲስ የሚገነባው ወደብ ወጪ በኢትዮጵያ እንደሚሸፈን ተገለጸ። ወደቡ በቀጥታ ከትግራይ ከሚነሳው አዲሱ የባቡር መስመር ጋር እንደሚገናኝም ታውቋል። እያደር ይፋ በመሆን ላይ ያሉት ፕሮጀክቶች አቶ ሃይለማርያም አስመራ ድረስ ለመሄድ ያሳዩትን ፈቃደኛነት “ለኢሳያስ የቀረበ የፖለቲካ አይስክሬም” በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተናገሩ፡፡ ባለፈው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የመሰረት ድንጋይ ለማስቀመጥ ጅቡቲ መጓዛቸውን የዘገቡት ያገር ውስጥ መገናኛዎች ያድበሰበሱት ጉዳይ ይፋ የሆነው ዲሰምበር 18/2012 ለአሜሪካ ሬዲዮ መግለጫ የሰጡት በመቀሌ ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ፖለቲካ ተንታኝና የታሪክ ምሁር የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር አየለ በከሬ ናቸው። ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋ እያደገ በመሄዱ ተጨማሪ ወደቦች እንደሚያስፈልጓት የጠቆሙት እኚሁ ምሁር በጅቡቲ የሚሰራው አዲሱ የታጁራ ወደብ … [Read more...] about ኢትዮጵያ በጅቡቲ ወደብ መገንባት ጀመረች
“እስክንድር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈታ”
አስራ ስድስት የአውሮፓ ፓርላማ አባላት የተፈራረሙበት የተላዘበ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ልከዋል። ደብዳቤው ጋዜጠኛ፣ አሳታሚና ጸሃፊ እስክንድር ነጋ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ባስቸኳይ እንዲፈታ የሚጠይቅም የሚያሳስብም ነው። ደብዳቤውን አስመልክቶ በዓለም ዙሪያ ላሉ የህሊና እስረኞች ጥብቅና የሚቆመው “የፍሪደም ናው” ነገረ ፈጅ ፓትሪክ ግሪፍተዝ ለቪኦኤ እንደተናገሩት እስክንድር ነጋ እንዲፈታ በመጠየቅ የተጀመረው ስራ እስክንድርን በማስፈታት እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል፡፡ እስክንድር ነጋ በየትኛውም መስፈርት ከሽብር ጋር የሚያገናኘው ጉዳይ እንደሌለ ማረጋገጣቸውን አስታውቀዋል። ህጉ የጋዜጠኞችን አፍ ለማዘጋት የተፈበረከ መሆኑንም አስታውቀዋል። አስራ ስድስቱ ፈራሚዎች በላኩት ደብዳቤ የእስክንድር ነጋን ቤት ለመውረስ ስለተጀመረው ሩጫ መረጃ እንዳላቸው አስታውሰው … [Read more...] about “እስክንድር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈታ”