አምስተኛ መካናይዝድ ክፍለጦር ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ እንደ ወትሮው ከዋርድያዋች ውጭ ሁሉም ተኝቷል። አንድ ታላቅ ፣ ጥቀር የሌሊት ልብሱን እንደ ለበሰ መፅሃፍ ያነባል ድንገት የቶክስ ድምፅ ሰማ በአካባቢው ሁሌም የቶክስ ድምፅ መስማት የተለመደ ቢሆንም ወታደር ነውና ምልልስ ካለ ብሎ ለማዳመጥ ሞከረ ከሁለት አቅጣጫ መሆኑን ተረዳ። ስልኩን አነሳ ወደተለያየ ቦታ ደወለ ሁሉም አይሰራም ስልኩን አየው ኔትወርክ የለውም አሁን ችግር እንዳለ ተራዳ ካለበት ክፍል ግድግዳ እየታከከ ወደ በሩ ተጠጋና በሩን ሲከፍተው የተመታ ጓዱ ከነክላሹ በጀርባው ወደቀ ወዲያው የቶክስ ሩምታ ወደ በሩ አቅጣጫ ተከፈተበት እንደምንም ከወደቀው ጓዱ ካላሹን ተቀብሎ እየተኮሰ በቅርብ ቀን ወደተሰራች የብሎኬት ግቢ ዘሎ ገባ። በግቢው ውስጥ አንደ ገባ የራሱ ጓድ የሆነች ሴት ወታደር በብሎኬት አጥር ቀዳዳ … [Read more...] about ትውስታ ዘ ዳንሻ – ታላቁ ጥቁር!
Opinions
የኔ ሃሳብ
ጥቁር ውሃ ላይ አስጨርሶ፣ እንደገና የፈረጠጠው ጄኔራል ከበደ ፈቃዱ ማን ነው?
የህወሃቱ ታጋይ ጄ/ል ከበደ በ1988 ዓም የ31ኛ ክ/ጦር 3ኛ ብርጌድ ፓራ ኮማንዶ፣ የ1ኛ ሻለቃ አዛዥ ሆኖ ሰርቷል። በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት በ31ኛ ክ/ጦር ምክትል ብርጌድ አዛዥ ሆኖ አገልግሏል። በ1992 ዓም 35ኛ ክ/ጦር ስትፈጠር የ35ኛ ክ/ጦር 3ኛ ብርጌድ አዛዥ ሆኖ ተሹሟል። በ1997 ዓም ኮር የሚባለው አጀረጃጀት ፈርሶ ዕዝ የሚባል አደረጃጀት ሲቋቋም፣ ግለሰብ የ35ኛ ክ/ጦር ም/አዛዥ ቀጥሎም የ33ኛ ክ/ጦር ዋና አዛዥ ሆኖ እስከ 2006 ዓ/ም ሠርቷል። በ2006 ዓ/ም እነ ጄኔራል አበባው ታደሰን ለማስወጣት በተደረገው ግምገማ፣ ግለሰቡ የአበባው አሽከር ነህ ተብሎ ተፈርጇል። ይህን ተከትሎም ከክፍለ ጦር አዛዥነቱ ተነስቶ፣ የዕዙ ማሰልጠኛ ት/ት ቤት አዛዥ ሆኖ ተመድቧል። የጡረታው ጊዜ ሲደርስ “ተጠቅሞ ይውጣ” ተባለና … [Read more...] about ጥቁር ውሃ ላይ አስጨርሶ፣ እንደገና የፈረጠጠው ጄኔራል ከበደ ፈቃዱ ማን ነው?
የትግራይ ጉዳይ፤ በረከተ መርገም!
የኢትዮጵያ መንግሥት ሰኔ 21 ቀን ያወጀውን የትግራይ ክልል የተኩስ አቁም አዋጅ በተመለከተ የተለያዩ ሀሳቦች እየተሠነዘሩ ይገኛሉ። እንደ እውነቱ ከሆነ መንግስት መተቸት ያለበት በመዘግየቱ ነው። የሕግ ማስከበር ዘመቻው በተጠቃለለ በሳምንታት ጊዜ ውስጥ የተኩስ አቁም አዋጁን አውጆ ወደ ፖለቲካዊ መፍትሄ ቢያመራ መልካም ነበር። ምናልባት ግን ከፊት ለፊቱ የነበረው ሐገራዊ ምርጫ ውሳኔውን እንዲያዘገይ እንዳደረገው ይታመናል። የኢትዮጵያ መንግስት ከዚህ በላይ የትግራይን ጉዳይ መሸከም አልነበረበትም። ቀድሞም የተለያዩ የውስጥና የውጭ አካላት ይሄንን ጉዳይ አንስተው ሞግተዋል። አውሮፓና አሜሪካ ጠንካራ ማእቀብ ለመጣል እየተዘጋጁ ነው። ይህ ማእቀብ የኢትዮጵያን ምርቶች እስካለመግዛት የሚደርስ ነው። ይህ ሁኔታ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከባድ ሸክም ነው። አሜሪካና የአውሮፓ ህብረት የትግራይ ችግር … [Read more...] about የትግራይ ጉዳይ፤ በረከተ መርገም!
ጩኸት ያፈናት ከተማ
የድምጽ ብክለት መጨመር የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ለምሬት እየዳረገ ይገኛል፡፡ ከመጠን ያለፉት ረባሽ ድምጾች፡- ከንግድ ትርኢቶች፣ ከሐይማኖት ተቋማት፣ ከምጽዋት ጠያቂዎች፣ ከጎዳና ላይ ንግድ፣ ከምግብና መጠጥ ቤቶች፣ ጋራዥ፣ እንጨት ቤት እና ብረት ቤትን ከመሰሉ አገልግሎት ሰጪዎች፣ ከፊልምና ሙዚቃ መሸጫዎች፣ ከተሽከርካሪዎች እና ከመሳሰሉት ይመነጫሉ፡፡ ለመሆኑ የድምጽ ብክለት ማለት ምን ማለት ነው? ምን ጉዳት ያስከትላል? እንዴት መቆጣጠር ይቻላል? የሚለውን ጥያቄ አንስተናል፡፡ በዚህ ጽሑፍ የባለሙያዎች አስተያየት እና የተጎጂዎች ሐሳብ ተካቷል፡፡ "የድምፅ ብክለት መደበኛውን የሕይወታችንን እንቅስቃሴ ይጎዳል፣ ያስተጓጉላል፣ እንቅልፍ ይነሳል፤ ውይይቶቻችንንና መደማመጣችንን ይቀንሣል፣ በአጠቃላይ የአኗኗራችን ሁኔታ የተረበሸ እንዲሆን ያደርጋል።” የሚሉት የቀድሞ የኢትዮጵያ … [Read more...] about ጩኸት ያፈናት ከተማ
ተፈትነን እንጂ ወድቀን አናውቅም
ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ፈተና ውስጥ ነን። ይሁን እንጂ እንደ ሀገር እና እንደ ህዝብ ተፈትነን እንጂ ወድቀን አናውቅም። “ኢትዮጵያን የመበታተኛው ሰአት አሁን ነው” - ግብጽና ሱዳን። ክፍል አንድ - መነሻ ሀገራችን የአፍሪካ የውሃ ማማ “the water tower of Africa” ይሏታል። ብዙ ሀይቆች አሏት፤ ብዙ ወንዞች አሏት። ምድር የተሸከመችው ትልቁ ወንዝ አባይ አላት። ብዙዎቹ የውሀ ሀብታምነታችንን ሲነግሩን እኛም ስንዘፍንለት፣ ለልጆቻችን በየተረቱና በየጂኦግራፊ ትምህርቱ ስናስተምረው ቆይተናል፤ ኖረናል። “አባይ አባይ፣ የሀገር ሀብት የሀገር ሰላይ” “አባይ ጉደል ብለው፣ አለኝ በትህሳስ፤ የማን ልብ ይችላል፣ እስከዚያው ድረስ።” ስለተፈጥሮ ሀብታችን ስንዘምርና ስንተርት አድገን፣ ሀገራችንን የድርቅና ረሃብ ምሳሌ ሆና መዝገበ ቃላት ውስጥ … [Read more...] about ተፈትነን እንጂ ወድቀን አናውቅም
ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም”
የቀድሞው ኢህአዴግ ካድሬዎች እና የህወሓት ጀነራሎች ሂሳብ አስተማሪው ኤርሚያስ ለገሰ ሆን ብሎ በቁጥር ሊጫወት ሞክሯል፡፡ አላማው ኢዜማ የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ሊያሸንፍ እንደማይችል አስመስሎ መሳል ነው፡፡ ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ ሆኖበት ነው፡፡ ኤርምያስ ሹመት አስቦ የለውጡ ደጋፊ የነበረ ጊዜ የተናገረው የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም፡፡ ምናልባት እንዲገባው ከዚህ በፊት ከነበረው የተቃዋሚዎች ዕጩዎች ቁጥር በ11% እድገት አሳይተናል እንበለው ይሆን?? ምንም እንኳን [ለእንደዚ አይነቱ አውቆ አበድ መፍትሄው] ንቆ መተው ቢሆንም ያቀረበውን የተንኮል መረጃ እንደ እውነት ሊወስዱ የሚችሉ ቅኖችን ከስህተት ለማዳን ዝርዝር መረጃውን ከዚህ በታች አቅርቤዋለሁ፡፡ ምርጫ የሚደረገው በዘጠኝ ክልሎች እና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች … [Read more...] about ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም”
ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር
እንደምን ሰነበታችሁ! እንኳን በጤና ተገናኘን! “በሚኖሩባት ሰዎች ክፋት የተነሳ ፍሬያማዋን ምድር ጨው አደረጋት” የሚል ቃል በቅዱሱ መጽሀፍ ውስጥ ሰፍሯል።ሕዝብ መቼም ቢሆን ክፉ ሆኖ አያውቅም፤ አይሆንምም። ነገር ግን ከሕዝብ የወጡ ጥቂቶች በዕኩይ ዓላማና ምግባራቸው ምድሪቱን ለጥፋት፣ ሕዝቡንም ለስቃይ ይዳርጋሉ። ይህንን ለማረጋገጥ ባህር ተሻግረን ማሳያ መፈለግ ሳይጠበቅብን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጭ ነኝ ባይ የነበረውን ትህነግን ማየት ይበቃል። ትህነግ ግማሽ ምዕት ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ በሕዝብ ትከሻ ላይ ተንጠላጥሎ፤ በሕዝብ ገላ ላይ እንደመዥገር ተጣብቆ የኢትዮጵያ ሾተላይ ሆኖ ኖሮ ሞቷል።ነጻነት ሳያውቅ ህዝብን ነጻ አወጣለሁ ብሎ ደደቢት ላይ የተፈለፈለው እፉኝት በሞቱ ለኢትዮጵያ ነጻነት ታውጇል። “ቀን ያስጎነበሰውን ቀን ቀና ያረገዋል” እንዲሉ የካቲት 11 ቀን … [Read more...] about ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር
አዲስ አበባ ብዙ ዋጋ የተከፈለባት ከተማ
1. መግቢያ፣ አዲስ አበባ ብዙ ዋጋ ተከፍሎባታል ሲባል ነገር ለማጣፈጥ የተነገረ ወሬ ሳይሆን በተጨባጭ የሆነና የተደረገ መሆኑን እኔ በህይወቴ ያየሁትን እንዲት ገተመኝ እንደ ምሳሌ ልጥቀስ። ስሜ ደረጀ ተፈራ ይባላል ተወልጄ ያደኩት አዲስ አበባ ፊትበር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው። ሰፈራችን ለታላቁ ቤተመንግስት (ምኒልክ ቤ/መ) ቅርብ በመሆኑ የደርግ ቅልብ ወታደሮችም ሆኑ የወያኔ አጋዚ ጦር የአካባቢውን ጸጥታ ለማስከበር ብቻ ሳይሆን ኮረዶችንም ለማሽኮርመም እኛ ሰፈር አይጠፉም ነበር። በደርግም ሆነ በወያኔ አገዛዝ ዘመን አንድ ነገር ኮሽ ባለ ቁጥር ከቤተ መንግስት፣ የደርግ ቅልቦችና የወያኔ አጋዚ ጦር፣ ከውጭ ጉዳይ ሚ/ር አና ከፓሊስ ገራዥ ደግሞ ፌዴራል ፖሊሶች ክላሻቸውን እያንቀጫቀጩ መጀመሪያ የሚመጡት እኛ ሰፈር ነበር። በዚህ ላይ ኮ/ል መንግሥቱ … [Read more...] about አዲስ አበባ ብዙ ዋጋ የተከፈለባት ከተማ
የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ወቅታዊ መግለጫ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ መስከረም 15/2013 ዓ.ም ባካሄደው ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባው፣ በከተማዋ የተጀመረውን ትምህርት ተሞክሮ እና አገልግሎቶች በአካታች ልማት (inclusive development) መርህ መሰረት አዲስ አበባ ዙሪያ ልዩ ዞን ወይም የኦሮሞ ብልጽግና “የፊንፊኔ ልዩ ዞን” በሚል መጠሪያ ባካተታቸው አካባቢዎች በሚገኙ 346 ትምህርት ቤቶች ውስጥ ለሚማሩ አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ(152,000) ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ የተማሪ ደንብ ልብስ፣ጫማ እና የትምህርት ቤት ምገባ አገልግሎት ለማቅረብ የሚያስችል 669,210,780 (ስድስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ሚልዮን ሁለት መቶ አስር ሽህ ሰባት መቶ ሰማንያ ብር) በጀት በመመደብ ለእርዳታ አገልግሎቱ እንዲውል በልዩ ሁኔታ ውሳኔ አሳልፏል። ፓርቲያችን ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያ … [Read more...] about የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ወቅታዊ መግለጫ
“In Honor and Remembrance of the Life of Professor Mesfin Woldemariam” Obang
Good Morning to everyone here. First of all, I would like to give my deepest sympathy to the family of Professor Mesfin Woldemariam and the great numbers of Ethiopians who consider him a great friend of the Ethiopian people for many generations. I also thank those who have given me the opportunity to speak today about one of greatest men I have been privileged to meet and know. This giant of a man has played an important and strategic role in my life and that of many others. Most people … [Read more...] about “In Honor and Remembrance of the Life of Professor Mesfin Woldemariam” Obang